Saturday, 17 March 2012 10:17

“መንታ ስሜት”፣ “ምኞቴ” እና “ስደት በጋዜጠኛው አይን” ለንባብ በቁ

Written by  መልካሙ ተክሌ (melkamutekele@gmail.com)
Rate this item
(0 votes)

በጌታቸው አበበ አየለ የተዘጋጀው “መንታ መንገድ” ታሪክ ቀመስ ልቦለድ መጽሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ በድሬዳዋ ተከስቶ የነበረው ጐርፍ ሰለባዎችን በመታሰቢያነት የዘከረው ዳጐስ ያለ መጽሐፍ፤ 408 ገፆች ያሉት ሲሆን በ50 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ በመምህርነት ሙያ የተሰማሩት ደራሲው ያዘጋጁት ከሁለት ሺህ ገጽ በላይ የሆነ “ጥበብ የአማርኛ መዝገበ ቃላት” በማሳተሚያ እጦት ምክንያት ሳይታተም መቅረቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በጥሩ ምንጭ ኪሩቤል የቀረበው “ምኞቴ” የግጥም መጽሐፍ ታትሞ ለገበያ ቀረበ፡፡ 93 ገፆች ያሉት መጽሐፍ 55 ግጥሞች የያዘ ሲሆን ዋጋው 20 ብር ነው፡፡ አብዛኛውን ግጥም ለተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች መታሰቢያ ያደረገው መጽሐፍ፤ ዛሬ በራስ አምባ ሆቴል ይመረቃል፡፡

ይህ በዚህ እንዳለ “ስደት በጋዜጠኛው ዓይን” የተሰኘ መፅሃፍ ታትሞ ሰሞኑን ለንባብ በቅቷል፡፡ ማህበራዊ ፖለቲካ ላይ ያተኮረው መጽሐፉ በ13 ክፍሎች በርካታ ርእሰ ጉዳዮችን ዳስሷል፡፡ የመጽሐፉ ደራሲ ነቢዩ ኢያሱ ካሁን ቀደም “አፍሪካና አምባገነን መሪዎቿ” ፣ “አረቦችና እስራኤል”፣ የእስራኤል የስለላ ውጤት” እና “የሕሊና ባርነት” የሚሉ መፃሕፍት ለንባብ አብቅቷል፡፡

 

 

Read 1996 times Last modified on Saturday, 17 March 2012 10:20