አብርሃም ግዛው ኢንተርቴይመንትና ስራዎች ድርጅት ከካሌብ ሆቴል ጋር በመተባበር ‹‹ድሮና ዘንድሮ›› የተሰኘ ዓለም አቀፍ የፍቅረኞች ቀንን ታሳቢ ያደረገ የመዝናኛ ፕሮግራም ማክሰኞ ይካሄዳል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ ታዋቂ ሰዎች፣ ረጅም ጊዜ በትዳር ያሳለፉ ጥንዶች የፍቅር ህይወታቸውን የሚያወጉበትና ልምድ የሚያካፍሉበት መድረክ መዘጋጀቱ የተገለፀ ሲሆን “የፍቅረኞች ቀን” በአገራችን መከበሩ ጥሩና መጥፎ ጎኑ ተነስቶ ውይይት ይደረጋል ተብሏል፡፡ በተጨማሪ አዝናኝ ገጠመኞች፣ ሙዚቃ፣ ትዊስትና ሳልሳ ዳንስ፣ ስታንዳፕ ኮሜዲና ሌሎችም የመዝናኛ ፕሮግራሞች ለታዳሚው እንደሚቀርቡ ለማወቅ ተችሏል።
Published in
ጥበብ