Saturday, 11 February 2017 13:35

የዓለማየሁ ገላጋይ ‹‹በፍቅር ስም›› ሰኞ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 የደራሲ፣ አርታኢና ሀያሲ ዓለማየሁ ገላጋይ ልብ ወለድ ‹‹በፍቅር ስም›› የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 11፡ 30 ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ ይመረቃል፡፡ በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ ኢ/ር ጌታሁን ሄራሞ፣ ቴዎድሮስ አጥላውና አሸናፊ መለሰ በመፅሐፉ ላይ ዳሠሳ የሚያቀርቡ ሲሆን በሀይሉ ገ/እግዚአብሔር - ወግ፤ ገጣሚ ኤፍሬም ስዩም - ግጥም እንደሚያቀርቡ የፕሮግራሙ አዘጋጅ ‹‹ተረት ፊልሞች›› አስታውቋል። መድረኩን የሚመራው ጋዜጠኛ ደረጀ ሀይሌ ነው
ተብሏል፡፡ ‹‹በዕለቱም በመፅሃፉ ሁለንተና ላይ ውይይት ይካሄዳል፡፡ እርስዎ መፅሃፉን ካላነበቡ እንብበው፣ ካነበቡ ተዘጋጅተው፣ እንዲያም ሲል እኔ ያነበብኩት የደራሲውን ቀደምት ልቦለዶች ነው ካሉ የመወያያ መድረኩ እርስዎንም ያሳትፋልና እንዳይቀሩብን›› ብሏል-ደራሲው በጥሪ ካርዱ ላይ ባሰፈረው ማስታወሻ፡፡

Read 2296 times