Sunday, 19 February 2017 00:00

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ሰዓት በማክበር ከአለም 11ኛ ደረጃን ዟል

Written by 
Rate this item
(7 votes)

ከአፍሪካ እና የመካከለኛው ምስራቅ አየር መንገዶች አንደኛ ደረጃን ይዟል

    የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ሰዓትን በማክበር ከአለማችን አየር መንገዶች 11ኛ፣ ከአፍሪካና ከመካከለኛው ምስራቅ አገራት አየር መንገዶች ደግሞ የ1ኛ ደረጃን መያዙን አለማቀፉ የአቪየሽን የመረጃ ተቋም “ፍላይትስታትስ” ሰሞኑን ባወጣው ወርሃዊ አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዲሱ የፈረንጆች አመት 2017 የመጀመሪያ ወር ካደረጋቸው 8 ሺህ ያህል በረራዎች 81 በመቶ ያህሉን ያጠናቀቀው፣ በረራዎቹን ለማጠናቀቅ ካስቀመጠው ጊዜ በ15 ደቂቃዎች ውስጥ መሆኑንም ተቋሙ በመግለጫው ጠቅሷል፡፡
አየር መንገዱ በበረራ ሰዓት አክባሪነት በአለማቀፍ ደረጃ ባስመዘገበው ከፍተኛ ውጤት ጥልቅ ደስታ ተሰምቶናል፤ ስኬቱ የአየር መንገዳችን የ12 ሺህ ትጉህ ሰራተኞች ጥረት ውጤት በመሆኑ ‹እንኳን ደስ አላችሁ› ለማለት እወዳለሁ ብለዋል፤ ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ ተወልደ ገብረ መድህን፡፡
“ሰዓቱን የጠበቀ በረራ ማከናወን የክቡራን ደምበኞቻችንን ፍላጎት በአግባቡ ለማሟላት ወሳኝ መሆኑን በአግባቡ እንረዳለን፤ ሁላችንም ሰዓቱን የጠበቀ በረራ እንዲኖር ለማስቻል ተግተን እየሰራን ነው” ሲሉም አክለዋል፡፡

Read 3882 times