Sunday, 19 February 2017 00:00

‹የተጣሉ ፊደላት›› የአጭር ልቦለድ መድበል ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 የደራሲ ሚካኤል መኮንን የአጭር ልቦለድ ስብስቦችን ያካተተ “የተጣሉ ፊደላት” የተሰኘ መፅሐፍ የፊታችን ሐሙስ ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ይመረቃል፡፡
    አጫጭር ልቦለዶቹ በህይወት ፍልስፍና፣ በአገርና በተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ ናቸው ተብሏል። ሰባት አጫጭር ልቦለዶችን የያዘው መፅሐፉ፤ በ242 ገጾች ተቀንብቦ፣ በ65 ብር ከ95 ሳንቲም ለገበያ ቀርቧል፡፡መጻህፍቱን ምስጋናው መፃህፍት መደብር እንደሚያከፋፍለውም ታውቋል፡፡

Read 2509 times