የደራሲ ሚካኤል መኮንን የአጭር ልቦለድ ስብስቦችን ያካተተ “የተጣሉ ፊደላት” የተሰኘ መፅሐፍ የፊታችን ሐሙስ ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ይመረቃል፡፡
አጫጭር ልቦለዶቹ በህይወት ፍልስፍና፣ በአገርና በተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ ናቸው ተብሏል። ሰባት አጫጭር ልቦለዶችን የያዘው መፅሐፉ፤ በ242 ገጾች ተቀንብቦ፣ በ65 ብር ከ95 ሳንቲም ለገበያ ቀርቧል፡፡መጻህፍቱን ምስጋናው መፃህፍት መደብር እንደሚያከፋፍለውም ታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና