Saturday, 18 February 2017 14:10

“ዳግማዊ ሂትለር” ለናዚው ጨፍጫፊ “ክብር ሰጥተሃል” በሚል ተከሰሰ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

 የፊቱን ገጽታ፣ አለባበሱን፣ አነጋገሩን፣ ስሙንና አጠቃላይ ሁኔታውን ሆን ብሎ ከአዶልፍ ሂትለር ጋር
በማመሳሰል፣ በየጎዳናው ሲንቀሳቀስ የነበረው ኦስትሪያዊ፤ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ፣ ለጨፍጫፊው ናዚ ክብር
ሰጥተሃል በሚል መከሰሱ ተዘግቧል፡፡ ሃራልድ ዜንዝ የሚለውን ወላጆቹ ያወጡለትን ስም ሃራልድ ሂትለር
ብሎ የቀየረው የ25 አመቱ ኦስትሪያዊ፤ ከጸጉር ስታይሉ አንስቶ፣ የጺም አቆራረጡንና አለባበሱን ከሂትለር ጋር
በማመሳሰል በየአደባባዩ ሲንቀሳቀስ መቆየቱን የጠቆመው ቢቢሲ፤ ጨፍጫፊውን ሂትለርን አክብረሃል በሚል
መከሰሱን ገልጧል፡፡     ግለሰቡ በመጽሃፍት መደብሮች እየተዘዋወረ የሁለተኛው የአለም ጦርነትን የተመለከቱ መጽሃፍትንና መጽሄቶችን በብዛት መግዛት ያዘወትር እንደነበር የጠቆመው ዘገባው፤ ሂትለር በተወለደበት ቤት አካባቢ በተደጋጋሚ ሲያንዣብብ መታየቱንም ጠቅሷል፡፡ ለሂትለር ክብር የሚሰጥ ድርጊት በአገሪቱ ህግ መሰረት ወንጀል መሆኑን የጠቀሰው ዘገባው፤ በብዙዎች ዘንድ “ዳግማዊ ሂትለር” ተብሎ የሚታወቀው ግለሰቡም፣ በተደጋጋሚ መሰል ድርጊቶችን ሲፈጽም መቆየቱ በምርመራ በመረጋገጡ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ፣ ክስ እንደተመሰረተበት አመልክቷል፡፡

Read 2129 times