Sunday, 19 February 2017 00:00

ናይጀሪያ በቦኮሃራም ጥቃት ከነዳጅ ገቢ 100 ቢሊዮን ዶላር አጥታለች

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 ናይጀሪያ አሸባሪው ቡድን ቦኮ ሃራም በነዳጅ ማጣሪያዎቿ ላይ በተደጋጋሚ ባደረሳቸው ጥቃቶች ሳቢያ በ2016 ከዘርፉ ማግኘት ከሚገባት ገቢ 100 ቢሊዮን ዶላር ያህል ማጣቷን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
    የሽብር ቡድኑ በአገሪቱ የነዳጅ ማምረቻ አካባቢዎች በሚፈጽማቸው ጥቃቶች ሳቢያ የናይጀሪያ የነዳጅ ምርት በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱን የነዳጅ ሚኒስትሩ ኤቢ ካቺክው ማስታወቃቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ በየዕለቱ የምታመርተው ነዳጅ በ1 ሚሊዮን በርሜል መቀነሱን ገልጧል፡፡
አገሪቷ ባለፉት 25 አመታት የከፋውን የኢኮኖሚ ድቀት ማስተናገዷንም የጠቀሰው ዘገባው፤ የአገሪቱ መንግስት የነዳጅ ምርቱን ለማሻሻልና ኢኮኖሚው እንዲያገግም ለማስቻል እየሰራ እንደሚገኝም ጠቁሟል፡፡

Read 1511 times