Saturday, 25 February 2017 13:13

የፎቶግራፍ ባለሙያው ነገ በአዳማ ይዘከራሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ላለፉት 50 ዓመታት በፎቶግራፍ ባለሙያነት የሰሩትና ባለፈው መስከረም 6 ቀን 2009 ዓ.ም በድንገተኛ ህመም ሀይወታቸው ያለፈው አቶ ተሾመ ንጉሴ ነገ ከቀኑ 10፡00 ጀምሮ በአዳማ ኩሪፍቱ ሪዞርት በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚዘከሩ የፕሮግራሙ አስተባባሪዎች ለአዲስ አድማስ ገለፁ፡፡ በዕለቱ የህይወት ታሪካቸውን የሚያስቃኝ ዘጋቢ ፊልም ግጥምና የህይወት ታሪካቸው የሚቀርብ ሲሆን የፎቶግራፍ ስራዎቻቸውን ለእይታ በማቅረብም እንደሚዘከሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 752 times