Saturday, 17 March 2012 10:49

የቦስተንና ለንደን ማራቶኖች ከፍተኛ ፉክክር ይታይባቸዋል

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(0 votes)

ከወር በኋላ የሚካሄዱት የቦስተንና የለንደን ማራቶኖች የኦሎምፒክ ሚኒማን ለማሟላት  ከፍተኛ ፉክክር እንደሚታይባቸው ተገለፀ፡፡ የኢትዮጵያና የኬንያ ምርጥ ማራቶኒስቶችን የሚያገናኙት ሁለቱ ማራቶኖች  በ2012 የለንደን ኦሎምፒክ ለሜዳልያ የሚጠበቁ አትሌቶች ፍንጭ እንደሚሰጥም ተገምቷል፡፡  የቦስተን ማራቶን ከወር በኋላ ሲካሄድ በሳምንቱ የለንደን ማራቶን ይቀጥላል፡፡በቦስተን ማራቶን ለሚያሸንፉ አትሌቶች በሁለቱም ፆታዎች ለእያንዳንዳቸው 150ሺ ዶላር የሚሰጥ ሲሆን በለንደን ማራቶን 50ሺ ዶላር ነው፡፡የቦስተን ማራቶን በ2011 በተደረጉ የዓለም ትልልቅ የማራቶን ውድድሮች አሸናፊ የሆኑ 5 ምርጥ ማራቶኒስቶችን ይሳተፉበታል፡፡

የኢትዮጵያ ሴት ሯጮች ባላቸው ወቅታዊ ብቃት ከፍተኛ ብልጫ እንደሚያሳዩ ግምት ተሰጥቷል፡፡የዱባይ ማራቶን አሸናፊዋ አሰለፈች መርጊያን ጨምሮ ገነት ጌታነህ፣ ማሚቱ ደስቃ፣ፍሬህይወት ዳዶ፤ አሹ ካሲምና ብዙነሽ ዳባ ይወዳደራሉ፡፡  በወንዶች ብቸኛው ኢትዮጵያዊ ተሳታፊ  ገብረእግዚአብሄር ገብረማርያም ነው፡፡  ከኬንያ አትሌቶች ከባድ ፉክክር ይጠብቀዋል፡፡ ገብረእግዚአብሄር ከ2 ዓመት በፊት የኒውዮርክ ማራቶንን ያሸነፈ ሲሆን አምና ደግሞ በቦስተን ማራቶን 3ኛ ደረጃ በማግኘት በ2 ሰዓት ከ04 ደቂቃ ከ53 ሴኮንድ በሆነ ጊዜ የግሉን ፈጣን ሰዓት አስመዝግቧል፡፡በተያያዘ በለንደን ማራቶን ፀጋዬ ከበደ፣ ፈይሳ ሌሊሳ፤ በዙ ወርቁ ማርቆስ ገነቴና አብርሃም ጨርቆሴ በወንዶች ምድብ ተሳታፊ ናቸው፡፡ በሴቶች ደግሞ አፀደ ባይሳ ፤እጅጋየሁ ዲባባ፣ ኮረኒ ጀሊላ ፤ብዙነሽ በቀለና አበሩ ከበደ ይሮጣሉ፡፡ በሁለቱ ትልልቅ የማራቶን ውድድሮች በኦሎምፒክ የማራቶን ቡድን ለመካተት ኢትዮጵያውያኑ ከኬንያውያን ብቻ ሳይሆን እርሰራሳቸውም ከፍተኛ ፉክክር ያደርጋሉ፡፡

 

Read 1970 times