Sunday, 26 February 2017 00:00

ሂትለር ሚሊዮኖችን ያስገደሉበት ስልክ 195 ሺህ ፓውንድ ተሸጠ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

     የናዚው መሪ አዶልፍ ሂትለር በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲገደሉ ትዕዛዝ አስተላልፈውበታል የተባለው ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ በአሜሪካ ሜሪላንድ ውስጥ በተካሄደ ጨረታ 195 ሺህ ፓውንድ መሸጡ ተዘግቧል፡፡
የሂትለር የጥፋት ሞባይል ተብሎ የሚጠራውና ከ70 አመታት በላይ ዕድሜ እንዳለው የተነገረለት ይሄው ቀይ ቀለም ያለው ስልክ፣ በስተጀርባው የሂትለር ስም፣ የንስር ምስል እና የስዋስቲካ ምክልት እንዳለበት የዘገበው ቢቢሲ፣ ስሙ ያልተገለጸ ተጫራች በስልክ ባቀረበው የመወዳደሪያ ዋጋ አሸንፎ እንደገዛው ገልጧል፡፡
ብርጋዴር ጄኔራል ራልፍ ራይነር የተባሉ እንግሊዛዊ የጦር መሪ እ.ኤ.አ በ1945 በርሊን ውስጥ የሚገኘውን የሂትለር ምሽግ በጎበኙበት ወቅት፣ ይሄው ታሪካዊ ስልክ ከሩስያ የጦር መኮንኖች በስጦታ መልክ እንደተበረከተላቸውም ዘገባው አስታውሷል፡፡

Read 3130 times