Monday, 27 February 2017 08:01

የአዘርባጃኑ መሪ ሚስታቸውን በምክትል ፕሬዚዳንትነት ሾሙ

Written by 
Rate this item
(8 votes)

    የአዘርባጃኑ ፕሬዚዳንት ኢሃም አሊየቭ የትዳር አጋራቸውን መህሪባንን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት አድርገው መሾማቸውን ባለፈው ማክሰኞ በይፋ ማስታወቃቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
   ፕሬዚዳንቱ የ52 አመት ዕድሜ ያላቸውን ባለቤታቸውን በአገሪቱ የስልጣን እርከን ሁለተኛ ደረጃን በሚይዘውና ባለፈው መስከረም ወር ላይ በጸደቀው አዲሱ የተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንትነት ቦታ ላይ ማስቀመጣቸው ብዙዎችን እያነጋገረ እንደሚገን የገለጸው ዘገባው፣ ዘገባው ገልጧል፡፡ ባለፈው መስከረም ወር
ላይ በተከናወነው ህዝበ ውሳኔ በአገሪቱ የህገ መንግስት አንቀጾች ላይ ማሻሻያ መደረጉን ያስታወሰው ዘገባው፣
የፕሬዚዳንቱን የስልጣን ዘመን ከአመስት አመታት ወደ ሰባት አመታት ማሳደጉ፣ ከ14 አመታት በፊት የአባታቸውን ቦታ ተክተው አገሪቱን መምራት የጀመሩት ፕሬዚዳንት አሊየቭ ከስልጣን ላለመውረድ የያዙት አቋም መገለጫ ነው በሚል መተቸቱንም አክሎ ገልጧል፡፡
   በምክትል ፕሬዚዳንትነት የተሾሙት መህሪባን በህክምና ሙያ ከዩኒቨርሲቲ መመረቃቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ ከዚህ ቀደም በህግ አውጭነት መስራታቸውንና የአንድ በጎ አድራጎት ድርጅት ሃላፊ ሆነው ማገልገላቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡
    ገና የ19 አመት ወጣት ሳሉ ከፕሬዚዳንት ኢሃም አሊየቭ ጋር ትዳር የመሰረቱት መህሪባን፣ በረጅም አመታት የትዳር ቆይታቸው ሁለት ሶቶች እና አንድ ወንድ ልጅ ማፍራታቸውን ዘገባው አክሎ ገለጧል፡፡

Read 4354 times