Monday, 06 March 2017 00:00

ስደት ላይ ያተኮረ የፖስተር ኤግዚቢሽን ዛሬ ይከፈታል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 “ስደት የሚለው ቃል በእርስዎ ምን ትርጉም አለው? አንድ ቀን እሰደዳለሁ ብለው ያስባሉ?” በሚሉና ሌሎች
ስለስደት የተነሱ ጥያቄዎች ላይ በዓለም ያሉ ከ40 በላይ ደራሲያንና ምሁራን የሰጧቸው መልሶች የተካተቱበት
የፖስተር ኤግዚቢሽን፣ ነገ በጀርመን የባህል ማዕከል (ጎተ) ከረፋዱ 4 ሰዓት ጀምሮ ይከፈታል፡፡
   በመክፈቻው ሥነ-ስርዓት ላይ ደራሲያን፣ ምሁራን፣ በስደት ላይ የሚሰሩ ድርጅቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የሚታደሙ ሲሆን ታዋቂው ደራሲ፣ ሀያሲና ጋዜጠኛ ዓለማየሁ ገላጋይና ደራሲ ሰዓዳ መሀመድ፤ “ስደት በኢትዮጵያ የስነ-ፅሁፍ ስራዎች ውስጥ እንዴት ይታያል” በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሁፎች እንደሚያቀርቡና ውይይት እንደሚደረግባቸው የጀርመን የባህል ማዕከል፣ የመረጃና የቤተ መፅሀፍት አገልግሎት ኃላፊ፣ አቶ ዮናስ ታረቀኝ ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡

Read 677 times