በደራሲ ዳንኤል ማሞ አበበ የተዘጋጀው ‹‹የኢጣልያ የመርዝ ጋዝ ጥቃትና የወቅቱ የምስራቅ አፍሪካ ሥጋት››
የተሰኘ መፅሀፍ ለንባብ በቃ፡፡ መፅሀፉ በጣሊያን ወረራ ጊዜ በመርዝ ጋዝ ጥቃት ሰለባ የሆኑትን ኢትዮጵያዊያን ማዕከል ያደረገ ሲሆን ስለ መርዝ ጥቃት አጀማመር፣ የኢጣሊያ የመርዝ ጥቃት በኢትዮጵያ፣ የኢጣሊያ ጦር ኢትዮጵያን ለመውረር ስላደረገው የኬሚካል ስልጠና፣ ከ1935 እስከ 1936፤ በኤርትራ ተከማችቶ ስለነበረው የኬሚካል ጋዝ፣ ስለ ሰሜን አፍሪካና ስለ አፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ስጋት… ታሪካዊ ዳራዎችን እያጣቀሰ የሚያስቃኝ ነው፤ ተብሏል፡፡ በሶስት ዋና ዋና ምዕራፎችና በበርካታንዑስ ምዕራፎች የተከፋፈለው መፅሀፉ፤ በ244 ገፆች ተቀንብቦ፣ በ81 ብር እየተሸጠ ሲሆን አበራ መፃህፍት መደብር እያከፋፈለው እንደሚገኝ ታውቋል፡፡
Monday, 06 March 2017 00:00
የኢጣሊያ የመርዝ ጋዝ ጥቃት በኢትዮጵያ ላይ
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና