68ኛው የግጥም በጃዝ ምሽት የፊታችን ረቡዕ በራስ ሆቴል ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል፡፡ በምሽቱ
ደራሲና ጋዜጠኛ ነቢይ መኮንንና ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ ግጥም የሚያቀርቡ ሲሆን አዜብ ወርቁ፣ የትነበርሽ ንጉሴ፣ ፀደንያ ገ/ማርቆስና ደስታ ነጋሽ ለታዳሚው ዲስኩር ያቀርባሉ ተብሏል፡፡ አርቲስት ሽመልስ አበራና እታፈራሁ መብራቱ አጭር ተውኔት እንደሚያቀርቡም አዘጋጆቹ ጨምረው ገልፀዋል፡፡
Monday, 13 March 2017 00:00
68ኛው ግጥም በጃዝ ረቡዕ ይካሄዳል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና