በህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ አተኩሮ የተሰራውና 90 በመቶ ትዕይንቱ ሱዳን ካርቱም ውስጥ የተቀረፀው
“እንቆጳ” ፊ ልም በ ግብፁ ሉ ግዞር ኢንተርናሽናል ፊ ልም ፌስቲቫል ላይ ለእይታ ሊቀርብ ነው፡፡
በደራሲ ተዋናይና ፕሮዲዩሰር ዩዲት ጌታቸው ተፅፎ በአለምፀሀይ በቀለና በአብርሀም ደምሴ ዳይሬክት የተደረገው ይሄው ፊልም፣ ለፌስቲቫሉ አዘጋጆች ከተለካ በኋላ ለ‹‹Official selection›› በመብቃቱ በፌስቲቫሉ ላይ ለመታየት ማክሰኞ ፊልሙ ወደ ካይሮ እንደሚያቀና ተገልጿል፡፡ በፊልሙ ላይ ሱራፌል ተካ፣ ዮዲት ጌታቸው፣ አለባቸው መኮንን፣ ደረጀ ደመቀና ሌሎችም እንደተሳተፉበት ታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና