ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ ከኢትዮጲስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ‹‹የኢትዮጵያ ታሪክ ጥያቄዎችና ባህሎች›› በተሰኘው የዶ/ር ኃብተማሪያም አሰፋ መፅሀፍ ላይ ነገ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በብሄራዊ ቤተ-
መፃህፍትና ቤተ-መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ውይይት ያካሂዳል፡፡
ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት ጋዜጠኛና የታሪክ ተመራማሪ ታዲዮስ ታንቱ እንደሆኑ የገለፀው ሚዩዚክ ሜይዴይ፤ መድረኩ በታሪክ ባለሙያው ሰለሞን ተሰማ ጂ. እንደሚመራ ጠቁሟል፡፡ በውይይቱ ላይ ፍላጎት ያለው ሁሉ እንዲሳተፍ አዘጋጁ ጋብዟል፡፡
Saturday, 11 March 2017 12:08
‹‹የኢትዮጵያ ታሪክ ጥያቄዎችና ባህሎች›› ላይ ነገ ውይይት ይካሄዳል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና