Monday, 13 March 2017 00:00

‹‹ፓርላማ፣ ታሪክ፣ ዴሞክራሲና ዲፕሎማሲ›› ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ለፌደሬሽን ምክር ቤትና ለክልል ምክር ቤት አባላት ስልጠና በመስጠት
የሚታወቁት አቶ መላኩ ሙሉዓለም ያዘጋጁት የፓርላማን ቀደምት ታሪካዊ አመሰራረት፣ ምንነትና አሰራርን የሚተነትነው ‹‹ፓርላማ፣ ታሪክ፣ ዴሞክራሲና ዲፕሎማሲ›› የተሰኘው መፅሀፍ የፊታችን ማክሰኞ ከምሽቱ 12፡00 ጀምሮ አምስት ኪሎ በሚገኘው በቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን አዳራሽ ይመረቃል፡፡ መፅሀፉ በተለይም ፓርላማ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የሚኖረው ፋይዳና ፓርላሜንታዊ ዲፕሎማሲን በሚመለከት ወቅታዊና ተጨባጭ መረጃዎችን አካትቶ ይተነትናል ተብሏል፡፡ በምርቃት ስነ-ስርዓቱ ላይ የሁለት ምክር ቤቶች ተወካዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙ ታውቋል፡፡

Read 1357 times