Monday, 13 March 2017 00:00

“አልቫሬጽ” የታሪክ መጽሐፍ እየተሸጠ ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 በአቶ ዮናስ ቦጋለ የተተረጎመውና የፖርቹጋላዊው ቄስ ፍራንሲስኮ አልቫሬጽ ጥንታዊና ታሪካዊ መጽሐፍ
“አልቫሬጽ በአጼ ልብነ ድንግል ዘመነ መንግስት ከ1520-1527 ወደ ኢትዮጵያ የተላከ የፖርቱጋል መልዕክት” በሚል ርዕስ ወደ አማርኛ ተመልሶ ለገበያ ቀርቧል፡፡ ደራሲው አባ ፍራንሲስኮ አልቫሬጽ፣ በዶን ሮድሪጎ ዴ ሊማ መሪነት የፖርቹጋሉን ንጉሥስ ዳግማዊ ዦአም መልዕክት ለአቢሲኒያው ንጉሥ እንዲያደርስ ከተላከው ልዑክ ጋር ተካፋይ የነበረ ቄስ ሲሆን በኢትዮጵያ በቆየባቸው ሰባት ዓመታት ውስጥ የታዘበውንና የአገሪቱን ሁለንተናዊ ገጽታ “Narrative of the Portuguese Embassy to Abyssinia 1520-1527” ሲል ጽፎታል፡፡
    መጽሐፉ የጥንታዊቷ ኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ገጽታ፤ የፖለቲካ አቅም፤ የኢኮኖሚና የባሕል ጥንካሬዋን በግልጽ ከማሳየቱም በላይ ለታሪክ ተማሪዎች፣ ባለሙያዎች እንዲሁም ጸሐፍት፣ ለመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች፣ ለማኅበረሰብ ጥናት ባለሙያዎች፣ ለጂኦግራፊ ጥናትና ለባህል ሰዎች ጠቃሚነቱ እጅግ ከፍተኛ ዋጋ ያለውና ተመራጭ እንደሚሆን ይታመናል ተብሏል፡፡ መጽሐፉ በጠራ ቋንቋና በግሩም አተራርክ፤ በሁለት መግቢያ፣ በሁለት ክፍል፣ ከመቶ በላይ በሆኑ ምዕራፎች የተዘጋጀ ሲሆን በ450 ገፆች ተቀንብቦ በ120 ብር ለአንባቢያን ቀርቧል፡፡

Read 1649 times