Monday, 13 March 2017 00:00

“ተልዕኮ አርማጌዶን” ገበያ ላይ ዋለ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

በደራሲና ጋዜጠኛ ተስፋፅዮን ጋሻነህ የተፃፈውና በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተው “ተልዕኮ አርማጌዶን” የተሰኘ ታሪካዊ ልቦለድ መፅሀፍ ሰሞኑን ገበያ ላይ ዋለ፡፡
     የመፅሀፉ ታሪክ መቼቱን ኢትዮጵያና ኤርትራ፣ ላይ አድርጎ በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት የአክሱም ፅዮን ታቦትን ለመዝረፍ በተደረገ ሙከራ ዙሪያ ያጠነጥናል። አንድነትና መቻቻል ለአገር ያለውን ከፍተኛ ፋይዳም እንደሚዳስስ የተነገረለት መፅሀፉ፤ መታሰቢያነቱ ለእውቁ የቀዶ ጥገና ሀኪምና ፖለቲከኛ ፕ/ር አሥራት ወልደየስ ተደርጓል፡፡ በ40 ምዕራፎች ተከፋፍሎ በ176 ገፆች የተቀነበበው ይህ መፅሀፍ፤ በ67 ብር ለገበያ የቀረበ ሲሆን ቀጣይ ክፍሉ በቅርቡ ለንባብ እንደሚበቃ ደራሲው ገልጿል፡፡

Read 2982 times