Print this page
Saturday, 11 March 2017 12:38

ዜድቲኢ የአሜሪካን ምርቶች ለኢራን በመሸጡ 1.1 ቢ. ዶላር ተቀጣ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 ኩባንያው አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለቺውን ማዕቀብ ጥሷል ተብሏል

       የቻይናው የቴሌኮም ኩባንያ ዜድቲኢ፣ አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለቺውን የንግድ ማዕቀብ በመጣስ በህገወጥ መንገድ የአሜሪካን የተለያዩ ምርቶች ለኢራን በመሸጡ ባለፈው ማክሰኞ 1.1 ቢሊዮን ዶላር ቅጣት እንደተጣለበት ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ኩባንያው የንግድ ማዕቀቡን በሚጥስ መልኩ የአሜሪካን የተለያዩ የኮምፒውተር ቴክኖሎጂ ምርቶች ወደ ኢራን መላኩ እንዲሁም ህጋዊ የኤክስፖርት ፈቃድ ሳይኖረው የአሜሪካ ምርቶች የሆኑ የሞባይል ቀፎዎችን ወደ ሰሜን ኮርያ እየላከ መሸጡ በምርመራ በመረጋገጡ በድምሩ 1.1 ቢሊዮን ዶላር ያህል ቅጣት እንደተጣለበት ዘገባው ገልጧል።
ዜድቲኢ እ.ኤ.አ ከ2010 እስከ 2016 በነበሩት አመታት 32 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ የአሜሪካ የኮምፒውተር ራውተር፣ ማይክሮፕሮሰሰርና ሰርቨር ምርቶችን ወደ ኢራን መላኩ መረጋገጡን የጠቆመው ዘገባው፤ በርካታ የአሜሪካ የሞባይል ቀፎ ምርቶችንም ለሰሜን ኮርያ ገበያ ማቅረቡን አስታውሷል፡፡
በአሜሪካ አራተኛው ግዙፍ የስማርት ፎን ሽያጭ ኩባንያ የሆነው የዜድቲኢ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዣኦ ሢያንሚንግ፣ ኩባንያው ጥፋቱን መፈጸሙን በማመን ሃላፊነቱን እንደሚወስድ የገለጹ ሲሆን  ዜድቲኢ በቀጣይ የንግድ አሰራሩን ለማሻሻል እንደሚሰራ ማስታወቃቸውን ዘገባው አስረድቷል፡፡

Read 1280 times
Administrator

Latest from Administrator