Monday, 20 March 2017 00:00

የህፃናት አምባ ልጆች የእርዳታ ማሠባሠቢያ ፕሮግራም አዘጋጁ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  የቀድሞ የህፃናት አምባ ውስጥ አድገው በተለያዩ የስራ መስክ በተሠማሩ ግለሠቦች የተቋቋመው ‹‹ትምህርት ለተቸገሩ በጎ አድራጎት ማህበር›› መጋቢት 10 ቀን 2009 ዓ.ም የገቢ ማሠባሠቢያ ፕሮግራም ያካሂዳል፡፡
ከ3 መቶ በላይ የትምህርት እድል ማግኘት ያልቻሉ ህፃናትን በኮተቤ ኪዳነምህርት ቤተ ክርስቲያን አካባቢ በከፈተው ትምህርት ቤት በማስተማር የሚታወቀው ማህበሩ፤ በአሁኑ ወቅት ይህን በጎ ተግባር ለማከናወን የአቅም ውስንነት ስላጋጠመው የእርዳታ ማሠባሠቢያ መርሃ ግብር ለማዘጋጀት መገደዱን አስታውቋል።
በዚህም መሰረት መጋቢት 10 ቀን 2009 ዓ.ም ከላምበረት አዲሱ መናኸሪያ ተነስቶ እስከ ኮተቤ ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን የ3.5 ኪሎ ሜትር የእግር ጉዞ በማዘጋጀትና የሙዚቃ ዝግጅትን አካቶ የገቢ ማሠባሠቢያ ሰፊ ፕሮግራም እንደሚያደርግ አስታወቆ፤ በእለቱ ድጋፍ እንዲደረግለት ጥሪ አድርጓል፡፡

Read 716 times