የዘንድሮ የአድዋ በዓልን አስመልክቶ ለአራተኛ ጊዜ የተካሔደው ከአዲስ አበባ አድዋ ‹‹ጉዞ አድዋ 4›› የእግር ጉዞ ከጥር 9 ጀምሮ የካቲት 23 ቀን 2009 ዓ.ም በደማቅ አቀባበል በአድዋ ከተማ መጠናቀቁ ይታወቃል፡፡ የእግር ጉዞውን በስኬት ያጠናቀቁ ተጓዦችን በደማቅ ስነስርዓት ለመቀበል
የፊታችን ሰኞ መጋቢት 11 ቀን ከምሽቱ 11፡45 ጀምሮ በአምስት ክሎ ብሔራዊ መዚየም ቅጥር ግቢ በሚገኘው ሉሲ ሬስቶራንት አዳራሽ፣ ልዩ ልዩ ኪናዊ ዝግጅቶችና የእራት ምሽት ተዘጋጅቷል፡፡
ለዘንድሮው ጉዞ አድዋ መሳካትና በሀገር አቀፍ ደረጃ የዓድዋ ክብረ በዓል ደማቅ እንዲሆን የላቀ ሚና ያበረከቱ የሚዲያ ተቋማትና ግለሰቦች የክብር አቀባበሉ ሥነስርዓት ተካፋይ ይሆናሉ ተብሏል፡፡
‹‹ጉዞ ዓድዋ›› በቀጣይ ዓመታት የአፍሪካ ተጓዦችን በእግር ጉዞው ለማሳተፍ ያለውን እቅድም በይፋ የሚገልጽበት ምሽት እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡
Published in
ዜና