Monday, 20 March 2017 00:00

አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ ደንበኞቹን ሸለመ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

    አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ ከትናንት በስቲያ በሸራተን ሆቴል በላኪነት፣ በአስጎብኚነት፣ በማማከርና በገንዘብ አስቀማጭነት የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ደንበኞቹ የሰርተፍኬትና በሦስት ደረጃ የዋንጫ ሽልማት ሰጠ፡፡
የፕላቲኒየም ተሸላሚ የሆኑት ድርጅቶች ካቤ ፒኤልሲ፣ የይርጋጨፌ የገበሬዎች ኅብረት ሥራ ማኅበራት ዩኒየን፣ ሐግቤስ ፒኤልሲና ግሪንላንድ ፒኤልሲ ሲሆኑ ሌሎችም የወርቅና የብር ዋንጫ ተሸልመዋል፡፡
አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ በአብዛኛው በኅብረት ስራ ማህበራት፣ እድሮች፣ አነስተኛ የብድር አቅራቢ ተቋማትና ግለሰቦች የተመሰረተ ሲሆን የባለአክሲዮኖቹም ቁጥር በቀጥታና በተዘዋዋሪ ከ300,000 በላይ ይሆናል፡፡
ባንኩ ከጊዜ ወደ ጊዜ የቅርንጫፍ ስርጭቱን በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች ለንግድ ስራ ምቹ በሆኑ ቦታዎች እያስፋፋ ሲሆን ሞባይልና ኢንተርኔት አገልግሎት ጨምሮ፤ ሁሉንም ቅርንጫፎቹን በመረጃ መረብ በማገናኘት ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑ ታውቋል፡፡



Read 948 times