Saturday, 25 March 2017 00:00

“ኢዮሃ ፋሲካ” ኤክስፖ ዛሬ ይከፈታል

Written by 
Rate this item
(3 votes)

 የትንሳኤን በዓል ምክንያት በማድረግ በኢዮሃ አዲስ ኢንተርቴይመንትና ኤቨንት የተዘጋጀው  “ኢዮሃ ፋሲካ” ኤክስፖ ዛሬ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ይከፈታል፡፡
ኤክስፖው ሻጭና ገዢን ከማገናኘት ባለፈ ለ22 ቀናት የሙዚቃ ኮንሰርቶችን በወጣትና አንጋፋ ድምፃዊያን በማቅረብ የመዝናኛና የፌስቲቫል ድባብ እንዲኖረው መደረጉን የኢዮሃ አዲስ ኢንተርቴይመንትና ኤቨንት ዋና ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ አዩ አለሙ ገልፀዋል፡፡
ከ400 በላይ የውጭ፣ 8 የአገር ውስጥ የንግድ ድርጅቶች ይሳተፉበታል የተባለው ይሄው ኤክስፖ፤አራት እውቅ ባንዶች የሚሳተፉበትና ከ100 በላይ ታዋቂ ዘፋኞች የሚያቀነቅኑበት የሙዚቃ ኮንሰርት፣ በዝነኛ ዲጄዎች የሚቀርብ ሙዚቃ፣ ከ80 በላይ ወጣቶችን የሚያሳትፍ  ዘመናዊና ባህላዊ የዳንስ ውድድር እንደሚቀርብበት ተጠቁሟል፡፡  
የፋሲካ ኤክስፖውን በየቀኑ ከ30 ሺህ በላይ፣ በጠቅላላ ግማሽ ሚሊዮን ህዝብ ይጎበኘዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ዋና ሥራ አስኪያጁዋ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡  
 ኢዮሃ አዲስ ኢንተርቴይመንትና ኤቨንት፤ በየቀኑ ወደ ኤክስፖው የሚመጡ ጎብኚዎች የሚገቡበትን ትኬት ቁጥር ለሽልማት ወደ 86 በአጭር መልዕክት በመላክ መኪና፣ ሞተር ሳይክልና ሌሎች ሽልማቶችን የሚያገኙበትን ዘመናዊ አሰራር ማመቻቸቱም ተነግሯል፡፡ የዚህን ዓመት የገና ኤክስፖ ጨምሮ ያለፈውን ዓመት የገናና የፋሲካ ኤክስፖዎች ያዘጋጀው ኢዮሃ፤ የዘንድሮን የፋሲካ ኤክስፖ ጨረታ በ13.6 ሚሊዮን ብር ማሸነፉ ታውቋል፡፡

Read 1496 times Last modified on Saturday, 25 March 2017 12:59