በደራሲ ታሪኩ ካሣሁን የተፃፈውና በፍቅር በማህበራዊና በመሰል ጉዳዮች ላይ 12 አጫጭር ታሪኮችን ያካተተው ‹‹ከእስከ›› መፅሐፍ ነገ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ ሆለታ በሚገኘው ኒያላ ሆቴል ይመረቃል፡፡በምርቃት ስነ-ስርዓቱ ላይ ወጣትና አንጋፋ ደራሲያንና ገጣሚያን ከአዲስ አበባ የተጋበዙ ሲሆን ስራዎቸውን እንደሚያቀርቡ የምርቃ ስነ-ስርዓት አስተባባሪው አቶ ጌታቸው አለሙ ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡ከእስከ፣ የተከፈለበት፣ ስድስተኛ፣ ከዚያም ከዚህም እና ሌሎችንም አጫጭር ታሪኮች ያካተተው መፅሀፉ በ120 ገፅ ተቀንብቦ በ45 ብር ለገበያ መቅረቡን አቶ ጌታቸው
ዓለሙ ጨምረው ገልፀዋል፡፡