ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ ከኢትዮጲስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ነገ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በብሔራዊ
ቤተ - መፃሕፍትና ቤተ - መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ፣ “ለራስ የተፃፈ ደብዳቤ” እና “የብርሃን ፍቅር” በተሰኙ
የገፃሚ ደበበ ሰይፉ የግጥም መድበሎች ላይ ውይይት ያካሂዳል፡፡ ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት ደራሲ
ዳንኤል ወርቁ እንደሆኑ የገለፀው ሚዩዚክ ሜይ ዴይ፤ ፍላጎት ያለው በውይይቱ ላይ እንዲሳተፉ ጋብዟል፡፡