Print this page
Friday, 07 April 2017 00:00

“ፈልጌ አስፈልጌ” ዛሬና ነገ በሁሉም ሲኒማ ቤቶች ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በደራሲ መላኩ ደምሰው ተፅፎ በአቦወርቅ ሀብቴ የተዘጋጀውና በአቡ ፊልም ፕሮዳክሽንና በአሰፋ ገረመው ፕሮዲዩስ የተደረገው “ፈልጌ አስፈልጌ” የተሰኘ ልብ አንጠልጣይ የቤተሰብ ድራማ ፊልም ዛሬና ነገ በሁሉም የግልና የመንግሥት ሲኒማ ቤቶች እንደሚመረቅ ተገለፀ፡፡ ፊልሙ በዋናነት አንድ አደራ የተሰጠው ወጣት አደራውን ለመወጣት የሚያደርገውን ውጣ ውረድና ፈልጎ አስፈልጎ የሚያገኘውን አደራውን የመጠበቅ መንገድ እንደሚያሳይ የፊልሙ ዳይሬክተርና ፕሮዲዩሰር አቶ የአቦወርቅ ሀብቴ ተናግረዋል፡፡ ሐሙስ ረፋድ ላይ በአዜማን ሆቴል ፊልሙን አስመልክተው ደራሲውና ፕሮዲውሰሩ በሰጡት መግለጫ፤ ፊልሙን ሰርቶ ለማጠናቀቅ 18 ወራትና 900 ሺህ መፍጀቱን ጠቁመው፤ የ1 ሰዓት 23 ደቂቃ ርዝመት እንዳለውም ተናግረዋል፡፡ በፊልሙ ላይ ተዘራ ለማ፣ ዝናህብዙ
ፀጋዬ፣ ፍ ፁም ፀ ጋዬ፣ ያ የህይራድ ማ ሞ፣ ኢ የሩሳሌም ደረጀ፣ ዳንኤል አበበ፣ ሀረግ መኳንንት፣ አማን ታዬ፣ መላኩ ደምሰውና ሌሎችም ወጣት ተዋንያን ተሳትፈውበታል፡፡ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የፊልም ባለሙያው ብርሃኑ ሽብሩ በወቅቱ የአገራችን ፊልም ተግዳሮቶችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ሙያዊ አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡

Read 933 times
Administrator

Latest from Administrator