Print this page
Monday, 10 April 2017 11:11

በግብጽ የ3ሺህ 700 አመት ዕድሜ ያለው አዲስ ፒራሚድ ተገኘ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 ከግብጽ መዲና ካይሮ በስተደቡብ በሚገኘው ዳሹር የተባለ አካባቢ በተደረገ ቁፋሮ፣ ከ3ሺህ 700 አመት በላይ ዕድሜ እንዳለውና የመጀመሪያው የጥንታዊ ግብጻውያን የልሙጥ ፒራሚድ ግንባታ ሙከራ ሳይሆን እንደማይቀር የተነገረለት አዲስ ፒራሚድ መገኘቱን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
ዳሹር በተባለውና ከፍተኛ የስልጣን ደረጃ ላይ የነበሩ ጥንታውያን ግብጾች መካነ መቃብር መገኛ መሆኑ በሚነገርለት በዚህ አካባቢ የተገኘው አዲሱ ፒራሚድ፤ ኮሪደሩን ጨምሮ የተወሰነ አካሉ በቁፋሮ መለየቱን የአገሪቱ የጥንታዊ ቅርሶች ተቋም ሃላፊ ማህሙድ አፊፊ ባለፈው ሰኞ ማስታወቃቸውን ዘገባው ገልጧል፡፡
አዲሱ ፒራሚድ በጥሩ ይዞታ ላይ እንደሚገኝ የአገሪቱ መገናኛ ብዙሃን መዘገባቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ የግብጽ የአርኪዎሎጂ ተመራማሪዎች በግኝቱ ላይ ተጨማሪ ጥናቶችንና የቁፋሮ ስራዎችን ለማከናወን በዝግጅት ላይ እንደሚገኙም አክሎ ገልጧል፡፡ በፒራሚዱ አካል ላይ ተጽፈው የተገኙ ጥንታዊ ጽሁፎች ይዘት በተመራማሪዎች በጥልቀት እንደሚጠናና፣ ጥናቱ ፒራሚዱን ማን አሰራው እና በየትኛው ስርወ መንግስት ወቅት ተሰራ የሚሉትን የመሳሰሉ ወሳኝ ጥያቄዎችን ለመመለስ ያስችላል ተብሎ እንደሚጠበቅም ዘገባው አስረድቷል፡፡

Read 1333 times
Administrator

Latest from Administrator