Saturday, 29 April 2017 13:57

የህዋ ሣይንስ ምሁሩ የቀብር ሥነ ስርዓት ተከናወነ

Written by 
Rate this item
(6 votes)

   በድንገተኛ የልብ ህመም ህይወታቸው ያለፈው የሥነ ህዋ ሣይንስ ተመራማሪውና የኢትዮጵያ የህዋ ሳይንስ ማህበር መስራች የነበሩት ዶ/ር ለገሠ ወትሮ፣የቀብር ሥነ ስርዓት ትናንት በአዲስ አበባ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን ተፈፅሟል፡፡
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፊዚክስ ትምህርት ክፍል መምህርና የሥነ ህዋ ሣይንስ ተመራማሪ የነበሩት ዶ/ር ለገሠ ወትሮ፤ለበርካታ አመታት በሥነ ህዋ ሳይንስ ላይ ግንዛቤ የሚያስጨብጥ የሬድዮ ፕሮግራም በማቅረብም ይታወቃሉ፡፡ የኢትዮጵያ ሣይንስ አካዳሚና የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማህበር መስራችም ነበሩ፡፡
የአለማቀፍ የአስትሮኖሚ ማህበር አባል የነበሩት ዶ/ር ለገሠ፤460 አመት የቆየውን የጂኦማግኔቲክ ፊልድ ሪቨርሳል እንቆቅልሽን በመፍታት እንደሚታወቁ ተጠቁሟል፡፡

Read 4031 times