በድንገተኛ የልብ ህመም ህይወታቸው ያለፈው የሥነ ህዋ ሣይንስ ተመራማሪውና የኢትዮጵያ የህዋ ሳይንስ ማህበር መስራች የነበሩት ዶ/ር ለገሠ ወትሮ፣የቀብር ሥነ ስርዓት ትናንት በአዲስ አበባ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን ተፈፅሟል፡፡
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፊዚክስ ትምህርት ክፍል መምህርና የሥነ ህዋ ሣይንስ ተመራማሪ የነበሩት ዶ/ር ለገሠ ወትሮ፤ለበርካታ አመታት በሥነ ህዋ ሳይንስ ላይ ግንዛቤ የሚያስጨብጥ የሬድዮ ፕሮግራም በማቅረብም ይታወቃሉ፡፡ የኢትዮጵያ ሣይንስ አካዳሚና የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማህበር መስራችም ነበሩ፡፡
የአለማቀፍ የአስትሮኖሚ ማህበር አባል የነበሩት ዶ/ር ለገሠ፤460 አመት የቆየውን የጂኦማግኔቲክ ፊልድ ሪቨርሳል እንቆቅልሽን በመፍታት እንደሚታወቁ ተጠቁሟል፡፡
Published in
ዜና