በጋዜጠኛ ደራሲና የቋንቋ መምህር ደሳለኝ ማሰሬ የተሰነደው ‹‹የፍቅር ሳቅ›› የግጥም ስብስብ መፅሀፍ ገበያ ላይ ዋለ፡፡ መፅሀፉ ወጣቱን መሰረት ባደረጉ ማህበራዊ፣ ባህላዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ ከ60 በላይ ግጥሞችን ማካተቱ የመፅሀፉ አዘጋጅ ጋዜጠኛ የቋንቋ መምህርና ደራሲ ደሳለኝ ማስሬ
ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡ በ96 ገፅ የተቀነበው መፅኀፉ በ40 ብር ከ50 ሳንቲም እየተሸጠ ሲሆን ደራሲው በቅርቡ ለንባብ የሚያበቃው የቋንቋ መፅሀፍ በመጠናቀቅ ላይ መሆኑንም ገልጿል፡፡