Print this page
Saturday, 06 May 2017 10:31

ፌስቡክ ጽንፈኞችን የሚያድኑ 3 ሺህ ሰራተኞችን ሊቀጥር ነው

Written by 
Rate this item
(3 votes)

  በፌስቡክ የማህበራዊ ድረገጽ በኩል ጽንፈኝነትን የሚያስፋፉና አንባቢያንን የሚያሸብሩ መልዕክቶችን የሚያሰራጩ ተጠቃሚዎችን የሚያድኑና እርምጃ የሚወስዱ ተጨማሪ 3 ሺህ ተቆጣጣሪ ሰራተኞችን ቀጥሮ ሊያሰማራ እንደሆነ ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፌስቡክ ተጠቃሚዎችን ወደ ጽንፈኝነት የሚስቡና የፍርሃትና የመሸበር ስሜትን የሚፈጥሩ መልዕክቶችና ቪዲዮዎች በከፍተኛ ሁኔታ እየተበራከቱ መምጣታቸውን ተከትሎ፣ የኩባንያው መስራች ማርክ ዙከርበርግ ጉዳዩን ለመግታት በማሰብ፣ ተጨማሪ ተቆጣጣሪዎችን ቀጥሮ ወደ ስራ እንደሚያስገባ ባለፈው ረቡዕ አስታውቋል፡፡
ተጠቃሚዎች መሰል መልዕክቶችንና ቪዲዮዎችን በፌስቡክ ላይ ሲያገኙ በአፋጣኝ ለኩባንያው 4ሺህ 500 ያህል ተቆጣጣሪዎች ጥቆማ መስጠት የሚችሉበት አሰራር ተቀይሶ እየተሰራበት እንደሚገኝ የተነገረ ሲሆን ኩባንያው ድርጊቱን በፈጸሙ ተጠቃሚዎች ላይ አፋጣኝ እርምጃ እንደሚወስድም ተነግሯል፡፡
ፌስቡክ በየሳምንቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መሰል ጥቆማዎችና የቅሬታ መልዕክቶች እንደሚደርሱት የዘገበው ዘ ጋርዲያን፣ እነዚህን በርካታ ጉዳዮች አጣርቶ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እንዲችል እስከ አመቱ መጨረሻ ድረስ ተጨማሪ 3 ሺህ ያህል ተቆጣጣሪዎችን ለመቅጠር ማቀዱንም ገልጧል፡፡

Read 1455 times
Administrator

Latest from Administrator