Print this page
Monday, 08 May 2017 00:00

እንግሊዝ ከአውሮፓ ህብረት ለመውጣት 100 ቢ. ዩሮ መክፈል አለባት ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የአውሮፓ ህብረት፤ እንግሊዝ ከህብረቱ አባልነት ለመውጣት ያከናወነቺውን ህዝበ ውሳኔ ተፈጻሚ ለማድረግና ጠቅልላ ለመውጣት በቅድሚያ 100 ቢሊዮን ዩሮ እንድትከፍል የሚያስገድድ መመሪያ ሊያወጣ እየተዘጋጀ ነው የተባለ ሲሆን፣ የብሬግዚት ሚኒስትሩ አገራቸው የተባለውን ክፍያ እንደማትፈጽም አስታውቀዋል፡፡
ህብረቱ እንግሊዝን ይህን ያህል ገንዘብ ለማስከፈል ማቀዱን ፋይናንሺያል ታይምስ ጋዜጣ ሰሞኑን መዘገቡን ተከትሎ፣ ሚኒስትሩ ዴቪድ ዴቪስ እንግሊዝ ክፍያውን አትፈጽምም ሲሉ በይፋ ማስታወቃቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
የእንግሊዝ መንግስት ይህን ያህል ገንዘብ እንዲከፍል ከአውሮፓ ህብረት በይፋ የቀረበለት ጥያቄ እንደሌለ የጠቆሙት ሚኒስትሩ፣ የተባለውን ክፍያ እንድንከፍል የሚያስገድዱ ህጎች እንዳሉና እንደሌሉ በዝርዝር ከመወያየት በዘለለ 100 በሊዮን ዩሮ አንከፍልም ሲሉም አክለዋል፡፡  
ህብረቱ እንግሊዝን 100 ቢሊዮን ዩሮ ያህል ገንዘብ ለማስከፈል ያቀደው ከአባልነቷ በመውጣቷ ሳቢያ የሚከሰቱ ወጪዎችን ለማካካስ ነው መባሉን የጠቆመው ዘገባው፣ የገንዘብ ክፍያው እንዲፈጸም ጥያቄውን ያነሱት አገራትም ፈረንሳይና ጀርመን ሊሆኑ ይችላሉ መባሉንም ገልጧል፡፡

Read 3256 times
Administrator

Latest from Administrator