Sunday, 07 May 2017 00:00

በሃሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የሚሰሩ 10 ሺህ ያህል ታንዛኒያውያን ተባረሩ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የታንዛኒያ መንግስት በሃሰተኛና በተጭበረበሩ የትምህርት ማስረጃዎችና የኮሌጅ ሰርተፍኬቶች አማካይነት በተለያዩ የመንግስት የስራ መደቦች ላይ ተቀጥረው ሲሰሩ የተገኙ 9 ሺህ 900 የአገሪቱ ሰራተኞችን ከስራ ገበታቸው ማባረሩ ተዘግቧል፡፡
የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ጆን ሙጉፋሊ ሙስናን ለመዋጋት በብሄራዊ ደረጃ ያወጁት ዘመቻ አካል በሆነው በዚህ እርምጃ፣ በመላ አገሪቱ በተከናወነ ምርመራ፣ በሃሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ተቀጥረው ሲሰሩ የተገኙት ከ9 ሺህ 900 በላይ የመንግስት ሰራተኞች በአስቸኳይ ከስራ እንደዲባረሩ መደረጋቸውን ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡
በተከናወነው የመንግስት ሰራተኞች የትምህርት ማስረጃ ማጣራት ስራ፣ የ1ሺህ 500 ያህል ሰራተኞች ትክክለኛ የትምህርት ማስረጃዎች በተጭበረበረ መልኩ እንደገና ተስተካክለው ለብዙ ሰራተኞች የትምህርት ማስረጃ ሆነው እንደቀረቡ መረጋገጡንም ዘገባው አመልክቷል፡፡
ባለፈው መጋቢት ወር ላይ በተከናወነ ተመሳሳይ ምርመራ፣ በስራ ገበታቸው ላይ ለሌሉ 20ሺ ገደማ ሰራተኞች ደመወዝ እንደሚከፈላቸውና በዚህም አገሪቱ በየአመቱ በአማካይ 82 ሚሊዮን ፓውንድ  እንደምታጣ መረጋገጡንም ዘገባው አስታውሷል፡፡

Read 1856 times