Print this page
Saturday, 06 May 2017 10:38

የወር አበባ መዛባት...

Written by 
Rate this item
(26 votes)

 ባለፈው እትም ስለወር አበባ መዘግየት መምጣትና መቅረት በሚመለከት አንዳንድ ነጥቦችን አንስተን ከዶ/ር ሙስጠፋ ነጋሽ ያገኘነውን ማብራሪያ ለአንባቢ ማለታችን ይታወሳል። ከወር አበባ ጋር በተያያዘ ያለውን ጠቃሚ ነገር ዶ/ር ሙስጠፋ ነጋሽ በቅዱስ ጳውሎስ ሚሊኒየም ኮሌጅ መምህርና የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስት የሆኑት ለዚህ እትም የሰጡትን ቁምነገር ታነቡ ዘንድ እነሆ ብለናል። ከ University of Maryland School of Medicine ድረገጽ ያኘነውን ቁምነገርም እናስነብባችሁዋለን።
የወር አበባ በተለይም ፍሰቱን ካልጠበቀ የሚያስትለው ችግር አለ።
የወር አበባ መጠን ከአስር እስከ ሰማንያ ሊትር በአማካይ ደግሞ ሰላላ ሚሊ ሊትር ነው። ከዚህ በተጨማሪም የሚፈሰው ደም የመርጋት ሁኔታ ሊታይበት አይገባም። ይህ ከሆነ ግን የወር አበባ መብዛቱን የሚያመላክት ነው። ስለዚህም ከዚህ ጋር ተያያዥ በሆነ ምክንያት፡-
የደም ማነስ እና ከደም ማነስ ጋር የተያያዙ ሌሎች ችግሮችንም ያስከትላል።
ልብ ድካምና ኢንፌክስን ለመሳሰሉት ሕመሞች ያጋልጣል።
የስነአእምሮአዊ ችግር ከወር አበባ ጊዜውን አለመጠበቅና የመጠን መብዛት ሊከሰት ይችላል። ለዚህም እንደ ምክንያት የሚቆጠረው አንዲት ሴት በአጠገብዋ ያለች ጉዋደኛ ወይንም እህትዋ የወር አበባዋ በትክክል የሚመጣና የሚሄድ ከሆነ እስዋ ግን እኔ ለምንድነው ይህ መዛባት የገጠመኝ በሚል ከመጨነቅ ሊከሰት ስለሚችል ነው። ስለ ዚህም ሐዘን፣ የስሜት መጎዳት፣ እንደድብርት የመሳሰሉት ችግሮችም ሊገጥሙአት ይችላሉ።
የወር አበባ መዛባት የሚያስከትለው ሌላው ችግር በተለይም በትዳር ላይ ላሉ ያልተጠ በቀ እርግዝና ነው። ከዚሀም የተነሳ ጽንሱን ወደማቋረጥ ስለሚሄዱ እና በተለያዩ ምክንያቶችም ለማህጸን ካንሰር የመጋለጥ እድሎችን ያስከትላል።
እንደ ዶ/ር ሙስጠፋ ነጋሽ ማብራሪያ ሴቶች የተለያዩ የእርግዝና መከላከያዎች በተለይም ፕሮጀ ስትሮን ያላቸው መከላከያዎችን ሲወስዱ የወር አበባ አይፈጠርም። በዚህም ምክንያት ብዙ ጊዜ እርግዝና ተፈጥሮ ይሆናል የሚል ስጋት በሴቶች ላይ ይስተዋላል። አንዳንዶች ደግሞ ደሜ ሆዴ ውስጥ እየተጠራቀመ ስለሆነ ሆዴን እየነፋኝ ነው የሚል ስጋት ይስተዋልባቸዋል። ነገር ግን ሁሉም ሰው ሊገነዘበው የሚገባው ነገር በመርፌ የሚወሰድ የእርግዝና መከላከያ የወርአበባ እንዳይፈጠር ማድረጉን ነው። ለዚህም ምክንያቱ አንዱን ሆርሞን ብቻ ስለሚይዝ ሲሆን በኪኒን መልክ የሚዘጋጁት ግን የወር አበባ በጊዜው እንዲመጣ የሚያስችሉ ሆነው የተዘጋጁ ናቸው። በእርግጥ በኪኒኒ መልክ የተዘጋጀ በመርፌ የሚሰጥ መከላከያ እንዳለ እሙን ነው። ስለዚህ የወር አበባ መጀመሪያ የመዛባትና መቅረት ችግሮች እስከ 49/አመት ባሉት እድሜ ውስጥ ከሆነ እርግዝና እና ከእርግዝና ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ችገግሮች መኖር ያለመኖራቸውን ማወቅ ተገቢ ይሆናል። በዚህ መልክ የሚከሰቱ ችግሮች ለሕይወት አስጊ ስለሚሆኑ እና ጊዜ ሊሰጣ ቸው ስለማይገባ በፍጥነት ወደሐኪም መሔድም ይመረጣል። ውርጃ የሚከሰት ከሆነ ኢንፌ ክሽን በመፍጠር ወደሰውነት ሊሰራጭ ከመቻሉም በላይ ማህጸንዋን ከጥቅም ውጭ ሊያደርግ ይችላል። ምናልባትም ከማህጸን ውጭ እርግዝና ከሆነ ከመጠን በላይ በሆድዋ ውስጥ ደም ስለሚፈስ ለሕይወት አስጊ ሊሆን ይችላል። በእርግጥ አንዳንድ ጊዜ የሚወሰዱ የእርግዝና መከላከያዎችም የወር አበባ መዛባቱን ሊያስከትሉ የሚችሉ ሲሆን ይህንን በሚመለከትም መድሀኒቱን ካዘዙ ባለሙያዎች ጋር መመካከር ያስፈልጋል።
የወር አበባ እርግዝና ሲኖር፣
ጡት በማጥባት ወቅት፣
በመርፌ መልክ የሚሰጡ የእርግዝና መከላከያዎች ሲወሰዱ ሊቋረጥ ይችላል።
ከላይ የተጠቀሱት ሁኔታዎች ተፈጥሮአዊ ሲሆኑ ተፈጥሮአዊ ያልሆነው ደግሞ፡-
እድሜው የወር አበባ መምጫ ሆኖ ሳለ ሳመጣ ሲቀር፣
ምንም የእርግዝና መከላከያ ሳይወሰድ፣
እርግዝና ሳይኖር፣
እድሜ ለወር አበባ መቋረጥ ሳይደርስ ከሆነ አሳሳቢ ይሆናል።
ስለዚህ አንዲት ልጅ ከ15-16/ ባለው እድሜዋ የወር አበባ ካላየች ወደሕክምና መሔድ ግድ ነው። የወር አበባ በትክክለኛው እድሜ ቢመጣም የመምጫ ጊዜውን የሚያዛባ ከሆነና የሚቋረጥ ከሆነም የህክምና ድጋፍ ያስፈልጋል።
በወር አበባ ምክንያት የሚመጣ ሕመምን በዘመናዊ ሕክምና ማስወገድ እንደሚቻል እና የተለያዩ የቤት ውስጥ እርዳታዎችም እንደሚያስወግዱት University of Maryland School of Medicine ድረገጽ ይገልጻል።
የመጀመሪያው የማህጸን አጥንት ተሸካሚ አጥንት ምርመራ ነው። ይህ የምርመራ ሂደትም ላፓራስኮፒ በሚባለው የምርመራ መሳሪያ የሚከወን ነው። ሌላው የህክምና ዘዴ የአልትራ ሳውንድ ምርመራ ነው። እንደዚሁም የደምና የሽንት ምርመራን በመውሰድ የተከሰተውን ችግር በዝርዝር ለማወቅ ይረዳል። የእርግዝና መከላከያ እንክብሎች ህመምን ለመቀነስ እና የተዛባ የወር አበባን ለማስተካከል ይረዳል ስለሚባል በሕክምናው ይታዘዛል። በሳይንሱ አለም ሌሎች የተለያዩ የህክምና ዘዴዎችም ስላሉ ችግሩ የገጠማቸው ሴቶች ወደሕክምናው አለም ጎራ እንዲሉ ይመከራል።
የወር አበባ መዛባትን በሚመለከት የተለያዩ የአመጋገብና የአኑዋኑዋር ምክሮችም ይለገሳሉ።
በካልሲየም የበለጸጉ ምግቦችን መመገብ ማለትም ቅጠላቅጠልና ጥራጥሬዎች እንዲሁም አትክልቶችን መመገብ ጠቃሚ መሆኑን ድረገጹ ያትታል።
ፍራፍሬዎች እንጆሪን እና ቲማቲምን ጨምሮ ባጠቃላይም ከሰውነት ውስጥ (Antioxidant) መመረዝን የሚያስወግዱ ምግቦችን መመገብ ጠቃሚ ነው።
በኢንደስትሪ ውስጥ ተሰርተው የታሸጉ እና እንደስንዴ ዳቦ፣ ፓስታ እና ስኩዋር የመሳሰሉትን ምግቦች ማስወገድ የወር አበባ መዛባት እንዳይኖር ያደርጋል።
ስጋን በሚመለከት የሚመከረው መጠኑ ትንሽ የሆነ ቀይ ስጋ እና ትንሽ ፋት ቅልቅል የሆነ ስጋን በመጠኑ መመገብን ይመክራል ድረገጹ።
ተጋግረው የታሸጉ ምግቦች እንደ ኩኪስ ኬኮች የተጠበሰ ድንች እና በኢንደስትሪ የተሰሩ ምግቦችን ማስወገድ ይጠቅማል።
በምግቦች ውስጥ የወይራ ዘይት፣ የአትክልት ዘይት የሆኑትን ለማብሰያነት መጠቀም ጠቃሚ ነው።
አልኮሆል እና ሲጋራ የሚጠቀሙ ከሆነ ማስወገድ ተገቢ ነው።
ከ6-8/ ብርጭቆ ውሀ በቀን መጠጣት ይመከራል።
በቀን እስከ 30/ደቂቃ የአካል አንቅስቃሴ ማድረግ ይመከራል።
ከዚህ ውጭ እንደከሞሜላ ያሉ ተፈጥሮአዊ የሆኑ ቅጠላ ቅጠሎች እንደሻይ አፍልቶ መጠጣትም ሊጠቅም ስለሚችል ከተለያዩ መረጃዎች በማገናዘብ እርግጠኛ የሆኑበትን ነገር መጠቀም ይመከራራል።
ከወር አበባ ጋር በተያያዘ አንዱ አስቸጋሪ ነገር የባህርይ መለዋወጥ ነው። ዶ/ር ሙስጠፋ ነጋሽ እንደሚሉት ሴቶች የወር አበባቸው ሊመጣ አካባቢ ባህሪያቸውን ብቻም ሳይሆን ሰውነታቸውም ጭምር ይለዋወጣል። የጡት ወጠርጠር ማለት፣ ጭንቀት፣ መነጫነጭ፣ ትውከት የመሳሰሉት ነገሮች ይከሰታሉ። ከዚህም በተጨማሪ የስሜት መለዋወጥ እና መረበሽ እንዲሁም የሆድ መክበድ ሊገጥማቸው ይችላል። የማህጸን ፈሳሽም በዛ ሊል ይችላል። በእነዚህ መሰል ምክንያቶች የተነሳ ትእግስትን የሚፈታተን ነገር ሊገጥማቸው ስለሚችል የባህርይ መለዋወጥ ነገር ሊታይ ይችላል። ከዚህ ውጭ ግን ሕመም የሚሆንበትም አጋጣሚ አለ። ሴትዋ ከስራራ እስከመ ቅረት ወይንም ወደሐኪም ቤት ሄዳ ሕክምና እስኪደረግላት ድረስ የሚያደርሳት ከሆነ ሕመም ስለሆነ በጣም አስቸጋሪ ነው። ስለዚህም አብረው የሚኖሩ ሰዎች የትዳር ጉዋደኛም ይሁን ቤተሰብ ይህንን መረዳትና ጊዜው እስኪያልፍ በትእግስት መጠበቅ ይኖርባቸዋል። ለዚህ ጉዳይ ምንም ግምት ሳይሰጡ ከሴትየዋ ጋር መጨቃጨቅ ወይንም ክብርን፣ ትኩረትን መንፈግ የበለጠ ስለሚያበሳጫት ሊጎዳት ይችላል። ይህ የገጠማት ሴት ደግሞ ምክንያቱን በመደበቅ ለመታገል መሞከር ሳይሆን ያለችበትን ወቅትና ሁኔታ በትክክል ማስረዳት መቻል አለባት። በግልጽ በመነጋገር ችግሩን መፍታት ይቻላል ይላሉ ዶ/ር ሙስጠፋ ነጋሽ የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስት እና መምህር።

Read 39956 times
Administrator

Latest from Administrator