Saturday, 13 May 2017 12:37

ሳኡዲ አረቢያ ግዙፍ የመዝናኛ ከተማ ልትገነባ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

መዝናኛው ኢንዱስትሪ የምታገኘውን ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ለማሳደግ ያቀደቺው ሳኡዲ አረቢያ፣ በአይነቱ ልዩ የሆነና የላስ ቬጋስን ያህል ስፋት ይኖረዋል የተባለውን ግዙፍ የመዝናኛ ከተማ ግንባታ ከስድስት ወራት በኋላ እንደምትጀምር መነገሩን ዘ ኢንዲፔንደንት ዘግቧል፡፡
ከመዲናዋ ሪያድ በስተደቡብ አቅራቢያ በሚገኝ 334 ስኩየር ኪሎ ሜትር ስፋት ያለው ስፍራ ላይ የሚቆረቆረውና በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር ወጪ የሚደረግበት ይህ ልዩ የመዝናኛ ከተማ፤ ለነዋሪዎችና ለውጭ አገራት ጎብኝዎች የተለያዩ የመዝናኛ፣ የስፖርትና የባህላዊ ትርዒቶች አገልግሎት እንደሚሰጥ ዘገባው አስታውቋል፡፡
እጅግ ማራኪ ፓርኮች እንደሚኖሩት የተነገረለት ይህ ግዙፍ መዝናኛ ከተማ፣ አለማቀፍ ተፈላጊነት እንደሚኖረውና ለአገሪቱ ከፍተኛ ገቢ ያስገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡
ሳኡዲ አረቢያ አዳዲስ የገቢ አማራጮችንና የኢኮኖሚ መስኮችን በማስፋፋት ኢኮኖሚዋን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ አቅዳ እየሰራች እንደምትገኝ የጠቆመው ዘገባው፤ የዚህ ጥረት አንዱ አካል የሆነው የግዙፍ የመዝናኛ ከተማ ግንባታ ፕሮጀክት በአራት አመታት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም አመልክቷል፡፡

Read 3270 times