Print this page
Sunday, 14 May 2017 00:00

በደቡብ ሱዳን የእርስ በእርስ ግጭት ከ2 ሚ. በላይ ህጻናት ተፈናቅለዋል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  በደቡብ ሱዳን ለአራት አመታት ያህል በዘለቀው የእርስ በእርስ ግጭት ሳቢያ በአገራቸው እና ከአገራቸው ውጪ የተፈናቀሉ የአገሪቱ ህጻናት ቁጥር ከ2 ሚሊዮን በላይ መድረሱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ማስታወቁን አልጀዚራ ዘግቧል፡፡
በአገሪቱ በታህሳስ ወር 2013 በተቀሰቀሰውና ይህ ነው የሚባል ዘላቂ መፍትሄ ሳይገኝለት ለአመታት በቀጠለው የእርስ በእርስ ግጭትና የፖለቲካ ቀውስ ሳቢያ ከ1.8 ሚሊዮን በላይ የአገሪቱ ዜጎች ወደ ኡጋንዳ፣ ኬንያ፣ ኢትዮጵያና  ሱዳን እንዲሰደዱ ማድረጉን  የጠቆመው ዘገባው፤ ከእነዚህ ስደተኞች መካከልም ከ62 በመቶ ወይም ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ህጻናት መሆናቸውን ገልጧል፡፡
የእርስ በእርስ ጦርነቱ ሌሎች ከ1 ሚሊዮን በላይ ደቡብ ሱዳናውያን ህጻናትንም በአገራቸው ውስጥ ከመኖሪያ ስፍራቸው ማፈናቀሉን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህጻናት መርጃ ድርጅትና የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን ማስታወቃቸውን ዘገባው አስረድቷል፡፡
የእርስ በእርስ ግጨቱ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ደቡብ ሱዳናውያን መገደላቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤በአገር ውስጥ እና ከአገር ውጭ የተፈናቀሉ አጠቃላይ ዜጎች ቁጥርም 3.5 ሚሊዮን እንደሚደርስ አስታውቋል፡፡

Read 1669 times
Administrator

Latest from Administrator