Sunday, 21 May 2017 00:00

በኮንጎ የተቀሰቀሰው ኢቦላ በአገሪቱ የከፋ አደጋ ጋርጧል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ከሶስት አመታት በፊት የተቀሰቀሰው አስከፊ የኢቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ 49 ዜጎቿን ለህልፈተ ህይወት በዳረገባት ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አንዳንድ አካባቢዎች ሰሞኑን የኢቦላ ቫይረስ ዳግም መቀስቀሱንና ይህም አገሪቱን ለከፋ ስጋት እንደዳረጋት የአለም የጤና ድርጅት አስታውቋል፡፡
ከሰሞኑ በአገሪቱ ሰሜን ምስራቃዊ አካባቢ በተቀሰቀሰው የኢቦላ ቫይረስ የተጠቁ ሁለት ሰዎች መገኘታቸውን፣ ሶስት ሰዎች መሞታቸውንና ሌሎች 18 ሰዎችም በቫይረሱ ሳይያዙ እንዳልቀሩ በመጠርጠሩ የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኙ ድርጅቱ አስታውቋል፡፡
በቫይረሱ ከተጠቁ ሰዎች ጋር ንክኪ አላቸው የተባሉ ከ400 በላይ ሰዎችን በአፋጣኝ ወደ ህክምና ካፕም ማስገባትን ጨምሮ፣ በአገሪቱ ኢቦላ ዳግም በወረርሽኝ መልክ እንዳይከሰት በመጪዎቹ ስድስት ወራት የተለያዩ ስራዎች እንደሚከናወኑ የዘገበው አሶሼትድ ፕሬስ፣ ለዚህም 10 ሚሊዮን ዶላር ያህል ያስፈልጋል መባሉን ገልጧል፡፡
ቫይረሱ ከታወቀበት እ.ኤ.አ ከ1976 አንስቶ ለሰባት ጊዜያት በወረርሽኝ መልክ በተከሰተባት ኮንጎ ሰሞኑን በአዲስ መልክ የተቀሰቀሰውን የኢቦላ ቫይረስ ስርጭት ለመግታት ችግሩ በተከሰተባቸው አካባቢዎች የህክምና ማዕከል ማቋቋምን ጨምሮ ሌሎች ርብርቦች እየተደረጉ እንደሚገኙም አስረድቷል፡፡

Read 901 times