Sunday, 28 May 2017 00:00

የኃይልዬ ታደሰ “በዘመኔ” አልበም ተመረቀ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   “በዘመኔ” የተሰኘውና የተለያዩ የሰርግ ዘፈኖችን ያካተተው አዲሱ የድምጻዊ ሃይልዬ ታደሰ አልበም፤ ከትናንት በስቲያ ምሽት በሳፋሪ አዲስ ሆቴል በተከናወነ ስነ-ስርዓት በይፋ ተመርቋል፡፡
ለድምጻዊው አራተኛ ስራው በሆነው በዚህ የሙዚቃ አልበም ውስጥ 9 የሰርግ ዘፈኖች የተካተቱ ሲሆን፣ ሞገስ ተካ፣ ቴዲ አፍሮ እና አሌክስ ይለፍ በዜማ ደራሲነት ሲሳተፉበት፤ በግጥም ደግሞ ሞገስ ተካ፣ መሰለ ጌታሁን፣ ይልማ ገብረ አብ እና ቴዲ አፍሮ ተሳትፈውበታል፡፡
ድምጻዊ ሃይልዬ ታደሰ በ1991 ዓ.ም ካወጣውና ከፍተኛ ተወዳጅነትን ካተረፈው “አንቺን ይዞ” ከተሰኘው የመጀመሪያ አልበሙ በተጨማሪ፣ “ሁሌ ሁሌ” እና “ፍቅር” የተሰኙ የሙዚቃ አልበሞቹን ለአድማጭ ማቅረቡ ይታወሳል፡፡
የድምጻዊው አድናቂዎች፣ ታዋቂ ድምጻውያንና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በተከናወነው የአልበሙ የምረቃ ስነስርዓት ላይ ድምጻዊውና ሌሎች ታዋቂ ድምጻውያን ስራዎቻቸውን ያቀረቡ ሲሆን ሌሎች ኪነጥበባዊ ዝግጅቶችም ተከናውነዋል፡፡

Read 1033 times