Sunday, 04 June 2017 00:00

ሒልተን አዲስ “የዓመቱ ምርጥ ሆቴል” ተባለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  አለማቀፍ የሆቴሎች ኔት ወርክ የተሰኘው ተቋም፤እንግዶች የሰጧቸውን የግብረ መልስ አስተያየት መነሻ በማድረግ፣ ሒልተን አዲስ ሆቴልን “የኢትዮጵያ የአመቱ ምርጥ ሆቴል” ሲል ሽልማት አበርክቶለታል፡፡
በመላው ዓለም በአለማቀፍ ሆቴሎች የሚጠቀሙ ደንበኞች በሚሰጡት የአገልግሎት እርካታ አስተያየት፤ ከኢትዮጵያ ሒልተን ሆቴል ጥሩ መስተንግዶ እንዳለው መመስከራቸውን ተከትሎ የእውቅና ሽልማት እንደተበረከተለት፣ የሆቴሉ የማርኬቲንግና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወ/ሮ ሃበን ክልሞን ለአዲስ አድማስ አስታውቀዋል፡፡ ለሽልማቱ ሆቴሉ ያለው አለማቀፍ እውቅና አስተዋፅኦ እንዳበረከተ ኀላፊዋ አልሸሸጉም፡፡  
ባለፈው ዓመት በተደረገው የኢትዮጵያ ሆቴሎች የደረጃ ምዘና፣ሒልተን አዲስ ባለ 3 ኮከብ ደረጃ ማግኘቱ አይዘነጋም፡፡

Read 1714 times