Saturday, 10 June 2017 14:26

አየር መንገድ ለ2ኛ ጊዜ የአፍሪካ የዓመቱ ምርጥ ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዘንድሮ ለ2ኛ ጊዜ የዓመቱ ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ ተባለ፡፡
ሰሞኑን በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ በተካሄደው 26ኛው ዓመታዊ የአየር መንገዶች ጉባኤና ኤግዚቢሽን ላይ አየር መንገዱ “ከአፍሪካ ሀገራት አየር መንገዶች ምርጡ መስተንግዶ አቅራቢ” ተብሎ ከአፍሪካ አቪዬሽን የእውቅና ሽልማት ተበርክቶለታል፡፡
አየር መንገዱ በተከታታይ ያስመዘገበውና እያስመዘገበ ያለው ፈጣን እድገት፣ ትርፋማነቱና ለአፍሪካ አቪዬሽን ኢንዱስትሪ ያበረከተው አስተዋፅኦ ተመራጭ እንዳደረገው ታውቋል፡፡ አየር መንገዱ፤ በርካታ ኩባንያዎችና አየር መንገዶች በከፍተኛ የፋይናንስ ችግር ውስጥ በወደቁበት ወቅት አቅሙን ማጠናከሩና የበለጠ ትርፋማ መሆኑም ተመራጭ አድርጎታል ተብሏል፡፡
ባለፈው የፈረንጆች ዓመት የ70 በመቶ ትርፍ ማስመዘገቡን የጠቀሰው የሽልማት ተቋሙ፤ 265 ሚሊዮን ዶላር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱንና የተጓዦችን ቁጥር ቀድሞ ከነበረው በ18 በመቶ ማሳደጉን ጠቁሟል፡፡

Read 1188 times