Monday, 12 June 2017 07:00

ብቃት ያላቸው የማህጸን ሐኪሞችን ለማፍራት

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ከተመሰረተ 25 አመት ሞልቶታል። በዚህ 25 አመት ጊዜ ውስጥ ምን ሰርቶአል? ሲባል ብዙ ክንውኖችን ማሳካቱ 25ኛ አመቱን ሲያከብር ተወስቶአል።
ለማስታወስ ያህልም ፡-
በስነተዋልዶ ጤና የሚያገለግሉ ሙያዊ ትንተናዎችን ለማቅረብ በአገር ደረጃ በሚዋቀሩ የተለያዩ ኮሚዎች ውስጥ በመሳተፍ ሁነኛ የሆነ አስተዋጽኦ አድርጎአል።
ባለፉት 25 አመታት ከ20 በላይ የሆኑ እጅግ ተጠቃሽ የሆኑ ፕሮጀክቶችን ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር አከናውኖአል።
ኤችአይቪ ከእናት ወደልጅ እንዳይተላለፍ ለመግታት ደረጃውን የጠበቀ ሕክምና እንዲሰጥ ከማድረግ አኩዋያ ወደ 70 የሚሆኑ የህክምና ድርጅቶች ውስጥ የሚገኙ ባለሙያዎችን ማሰልጠንና በተጨማሪም ክትትል በማድረግ የበኩሉን ሚና ተጫውቶአል።
በመካከለኛ ደረጃ የሚገኙ የጤና ባለሙያዎችን በማዋለድ ተግባር ላይ የተሸለ ክህሎት ኖሮአቸው በተለይም በኦፕራሲዮን መውለድ የሚያስፈልጋቸውን እናቶች ከመደገፍ አኩዋያ ቁጥራቸው ወደ 47 ለሚሆኑ የጤና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቶአል። ይህ ስልጠና እስከ 6 ወር የደረሰ ተከታታይ ስልጠና ሲሆን በተለይም እስፔሻሊስት ሐኪሞች በማይገኙበት ቦታ ለወላድ እናቶች ባለሙያው አስፈላጊውን እገዛ ሊያደርግ የሚችልበት ስራ ተሰርቶአል። በዚህም ፕሮጀክት እስከ መቶ ሺህ እናቶች ተጠቃሚ ሆነዋል።
በወሲባዊ ጥቃት እና ትንኮሳ ዙሪያ በተለይም ሴቶች ጥቃቱ ከደረሰባቸው በሁዋላ ተገቢውን ሕክምና እንዲያገኙ እና ክትትል እንዲደረግላቸው የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን በአዲስ አበባና በተለያዩ መስተዳድሮች ዋና ዋና ከተሞች ውስጥ 6 ሞዴል ክሊኒኮችን በመመስረት ደረጃውን የጠበቀ ሕክምናና እንክብካቤ እንዲያገኙ አድርጎአል።
በማደግ ላይ ባሉ ክልሎችና በአርብቶ አደሮች አካባቢ የማህረሰቡን የስነተዋልዶ እውቀ ትና ግንዛቤ ከማሳደግ አኩዋያ የሚሰሩ ስራዎች ያሉ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም ሙያተ ኞች እርህራሔንና ተገቢ የሆነን የህክምና እርዳታ ለተገልጋዩ ለማዳረስ የሚችሉበትን ስልጠና ማህበሩ በመስጠት ላይ ነው።
ማህበሩ ከ20 በላይ የሚሆኑ ሙያነክ መመሪያዎችን በማዘጋጀት ደረጃውን የጠበቀ ግልጋሎት ለማህበረሰቡ እንዲሰጥ ሲያደርግ ቆይቶአል።
ከላይ ያነበባችሁት እውነታ በማህበሩ ፕሬዝዳንት ዶ/ርደረጀ ንጉሴ የተገለጸ ነው። የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር በ25 አመታት ውስጥ እንዳካበተው ልምድ አሁንም የእናቶች ንና ጨቅላዎቻቸውን ጤንነትና ሕይወት ለመጠበቅ የሚያስችሉ ፕሮጀክቶችን ነድፎ ከተለያዩ ድጋፍ አድራጊ ድርጅቶች ጋር በመስራት ላይ ይገኛል።በኢትዮጵያ እናቶች በሰለጠነ የሰው ኃይልና በተገቢው ደረጃ በጤና ተቋም አገልግሎት እንዲያገኙ ያስፈል ጋል ሲባል አንዳንድ እንደችግር የሚታዩ ነገሮችን መንቀስ ወይንም እንዲወገዱ ማድረግ ያስፈልጋል። ይህንንም በሚመለከት ከታቀዱ ስራዎች መካከል ከአሜሪካው የጽንስና ማህጸን ሕክምና ኮሌጅ ጋር በመተባበር የሚሰራው ይገኝበታል።
 በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በተለያየ ደረጃ ላይ የሚገኙ አዳዲስና ነባር ዩኒቨርሲቲዎች በጠቅላላ ሐኪምነት ሙያ የተሰማሩ ባለሙያዎችን በልዩ ሙያ የማህጸንና ጽንስ ሕክምናን በማሰልጠን ላይ ይገኛሉ። ነገር ግን እነዚህ የተለያዩ ተቋማት በተመሳሳይ ደረጃ ላይ ስለማይገኙ አገሪቱ የምታፈራቸው ባለሙያዎች የተለያየ ደረጃ እንዲኖራቸው ስለሚያደርግ ጥራት ያለው እና በተመሳሳይ ደረጃ ብቃት ያለው ሕክምና ከመስጠት አኩዋያ ክፍተት እንዲመጣ ያደርጋል። ስለዚህም ይህንን ክፍተት በዋነኛነት በተሻለ ደረጃ መሙላት አስፈላጊ ሲሆን ይህንንንም የትም ህርት እና ሙያ ጥራትና ብቃት ለማምጣት እንዲያስችል የፌደራል ጤና ጥበቃ ሚኒስ ር በአምስት አመቱ የጤናው እቅድ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። ከዚህም በመነሳት የማህ ጸንና ጽንስ ሕክምና ተማሪዎች በተሻለ ዝግጅት ሰልጥነው እንዲወጡ ማድረግና ስራ ላይ ያሉ ደግሞ የተሻለ ተከታታይ ትምህርት እንዲያገኙና ከዚህ በሁዋላ በእነዚህ ዝግጅቶች አማካ ኝነት ለተገል ጋዩ ሕዝብ ጥራቱን የጠበቀ ግልጋሎት መስጠት እንዲያስችላቸው ማድረግ አንዱ ግብ ነው።
የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ከአሜሪካው የጽንስና ማህጸን ሕክምና ኮሌጅ ጋር በመተባበር ለመስራት እቅድ ከያዘባቸው ፕሮጀክቶች አንዱ ሐኪሞችን በብቃት እና በተመሳሳይ ደረጃ ማስተማር በመሆኑ በፈረንጆቹ አቆጣጠር ጁን 5-6 ማለትም ግንቦት 28 -29 በአዲስ አበባ በተለያዩ መስተዳድር የሚገኙ ከ12 ድህረ ምረቃ ተቋማት ለተወከሉ የድህረ ምረቃ ዳይሬክ ተሮች ለሆኑ የጽንስና ማህጸን ሕክምና ባለሙያዎች ስልጠናውን ሰጥቶአል። እንደ ዶ/ርባልካ ቸው ንጋቱ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ኮሌጅ መምህርና ተባባሪ ፕሮፌሰር የጽን ስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስት የድህረ ምረቃ ፕሮጀክት አስተባባሪ ገለጻ የድህረ ምረቃው ትምህርት በየተቋማቱ በተለያየ መንገድ ይሰጥ የነበረ ሲሆን መመራት ያለበት ግን በራሳችን ሀገራዊ ሁኔታ በመመስረት የፕሮግራሙን ባህል ሳይለቅ ነገር ግን መሰረታዊ የሆኑ ሳይንሳዊ ነገሮችን ሁሉም ጋ አንድ አይነት ለማድረግ ነው የስልጠናው ዋና አላማ።
በተለይም ስልጠናው ያስፈለገበት ምክንያት በአገሪቱ ውስጥ በሚካሄዱ የማህጸንና ጽንስ ድህረ ምረቃ ትምህርቶች ላይ የሚካሄዱ እንቅስቃሴዎች መዋቅራዊ ለውጥ እንዲያመጡ እና ትምህ ርቱ አግባብ ባለው መንገድ በመላ ሀገሪቱ ባሉ የትምህርት ተቋማት ወጥ የሆነ የትምህርት ሂደት እንዲኖራቸው ለማገዝ ነው። በዚህ ረገድም ለስልጠናው የተጋበዙት የየፕሮግራሙ ዳይሬክተሮች ሲሆኑ ለስልጠናውም ከአሜሪካው የጽንስና ማህጸን ትምህርት ኮሌጅ ጋር በመተባበር ባለሙያዎች ተጋብዘው አስፈላጊውን ሳይንሳዊ እውቀት አስጨብጠዋል። ይህ ስልጠና በድህረ ምረቃ ትምህርት ላይ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ነገሮችን በምን አይነት መንገድ ሁሉም ቦታ ያሉ የድህረ ምረቃ አስተባባሪዎች መያዝ አለባቸው የሚለውን ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ በማሳየት ከድህረ ምረቃ ተማሪዎች አቀባበል እስከ ተመርቆ መውጣት ድረስ ያለው ሂደት በምን መንገድ መመራት አለበት? ምን አይነት ችግሮች ሊያጋጥሙ ይችላሉ? ችግሮች ሲያጋጥሙስ እንዴት ነው መፍታት የሚቻለው? ከየትምህርት ተቋማቱስ ሊደረግ የሚገባው ድጋፍ ምንድነው? ተማሪዎቹስ በየአመቱ ማወቅ ያለባቸው የትኞቹን ነገሮች ነው? እነዚህን ነገሮች እያገኙ መሆናቸውን እንዴት መከታተል ይቻላል? የሚሉትና የመሳሰሉት ነገሮች ትኩረት ተሰጥቶአቸው ስልጠና ተሰጥቶአል።
እንደ ዶ/ርባልካቸው ማብራሪያ ከአሁን ቀደም ፕሮግራሞቹ ይመሩ የነበሩት በባህላዊ መንገድ ነበር ማለት ይቻላል። ነገር ግን ተማሪዎቹ የአራት አመት ቆይታቸውን በምን መንገድ ስርአት ባለው መልክ በሁሉም ተቋማት በተመሳሳይ ሁኔታ መምራት ይገባል የሚለው የዚህ ፕሮጀክት ዋናው ማጠንጠኛ ነው። በኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሕክምና ባለሙያዎች ብዛት በጣም ውስን በመሆኑ ተገልጋዩን ለመድረስ በማይችልበት ሁኔታ ይገኛል።
በኢትዮጵያ ካሉት የጽንስና ማህጸን ሕክምና ባለሙያዎች 65ኀየሚሆኑት በአዲስ አበባ የሚሰሩ ናቸው።
ቀሪዎቹ 35 ኀየሚሆኑትም የሚገኙት በየመስተዳድሩ ትልልቅ ከተሞች እንደ መቀሌ ፣አዋሳ ፣አዳማ በመሳሰሉት ነው።
ከላይ በተመለከተው መረጃ መሰረት የህክምና ባለሙያዎችን ብቃት እና ብዛት ማግኘት ወሳኝ ሁነት ነው። ይህ የድህረ ምረቃ ትምህርት ደግሞ የባለሙያዎችን ቁጥር ለማሳደግ እና አገል ግሎቱንም በመላ አገሪቱ በተመሳሳይ ሁኔታ እንዲዳረስ ለማድረግ እንደሚያስችል እሙን ነው። የአሜሪካው የጽንስና ማህጸን ሕክምና ኮሌጅ ከኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ጋር ለጀመረው ፕሮጀክት በአሜሪካ ዳይሬክተር በመሆን የሚሰሩት ዶ/ርብርሀኑ ታደሰ ሀሳባቸውን እንደሚከተለው ገልጸዋል።
“...የአሜሪካው የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ከኢትዮጵያው የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ጋር በመተባበር ከሚሰራው ስራ አንዱ የማህጸን ሐኪሞች ስልጠናን ማገዝ ነው። በዚህም ፕሮግራሙ የድህረ ምረቃው ትምህርት በሚሰጥባቸው በሁሉም ተቋማት ያሉ ዳይሬክተሮችን እውቀት ከፍ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ ስልጠና ነው። ተማሪዎቹ መሰልጠ ናቸው በትምህርት እና በስራ ጥራታቸው ብቁ መሆናቸው በኢትዮጵያ ለሚሰጡት አገልግሎት ብቻም ሳይሆን በመላው አለም ተገኝተው ብቃት ባለው መንገድ መስራት እንዲችሉ ያደርጋቸ ዋል። ስለዚህም ለስልጠናው የተጋበዙት በትምህርት ቤቶቹ ውስጥ ፕሮግራሙን የሚመሩ ዳይሬክተሮች በመሆናቸው የተሻለ አመራር መስጠት እንዲችሉ የሙያ ብቃታቸውን የሚያዳብር ስልጠና ነው። ስልጠናው የማህጸን ሐኪሞች ለመሆን የድህረ ምረቃ ትምህርታቸውን ለሚከታ ተሉ ሁለገብ የሆነ ድጋፍ በመስጠት በመርሐ ግብሩ ውስጥ በጥራት የሚወጡበትን መንገድ የሚያመቻች የአመራር ክህሎት ስልጠና ነው። ይህንን ስልጠና ለመስጠት የመጡት ሶስቱም ባለሙያዎች በአሜሪካ ከፍተኛ ሙያ ያላቸው ፕሮፌሰሮች ሲሆኑ ለአሜሪካ ሐኪሞች የሚሰጠ ውን ስልጠና በተመሳሳይ ደረጃ ኢትዮጵያ ላሉት ባለሙያዎችም እየሰጡ ነው። ስለዚህም ከትምህርቱ ጋር በተያያዘ ልምዳቸውንም ያካፍላሉ።”

Read 1793 times