Print this page
Sunday, 18 June 2017 00:00

የስደተኞች ቀን በአለማቀፍ ደረጃ ማክሰኞ በኢትዮጵያ ይከበራል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 1700 ስደተኞች በ20 ዩኒቨርሲቲዎች በነፃ እየተማሩ ነው

     ከ850 ሺህ በላይ የተለያዩ ሀገራት ስደተኞችን ማስተናገዷ ያስመሰገናት ኢትዮጵያ፤ የዘንድሮውን የዓለም የስደተኞች ቀን በዓል የተመድ የስደተኞች ኮሚሽነር በተገኙበት የፊታችን ማክሰኞ በጋምቤላ ታስተናግዳለች ተብሏል፡፡ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ስደተኛ በማስተናገድ ከአፍሪካ ቀዳሚ የሆነችው ኢትዮጵያ፤ በስድስት የሀገሪቱ ክልሎች 27 የስደተኛ መጠለያዎችን አቋቁማ ማስተናገዷ እውቅና ተሰቶት “we
stand together with refugees” በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን በዓል እንድታስተናግድ እድል ማግኘቷን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል፡፡
“ስደተኞች እንደሀገሬው ዜጎች የሚኖሩባት ሀገር ነች ኢትዮጵያ” ያለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ በ20 ዩኒቨርሲቲዎች ለ1700 ስደተኞች ነፃ የትምህርት እድል ተሰጥቷቸው በመማር ላይ መሆናቸውንም አስታውቋል፡፡ ኢትዮጵያ በአሉን እንድታዘጋጅ የተመረጠችው በአለም አቀፍ ደረጃ ከስደት ጋር ተያይዘው እየተከሰቱ ባሉ ችግሮች መፍትሄ ዙሪያ ኃላፊነት በመሸከም ችግሩን ለማጋራት ባሳየችው ቁርጠኝነት ነው ተብሏል፡፡

Read 1243 times
Administrator

Latest from Administrator