Sunday, 25 June 2017 00:00

ጌት ፋም ሆቴል ባለ 5 ኮከብ ደረጃን አገኘ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

     ከሁለት ዓመታት በፊት ተከፍቶ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው ጌትፋም ኢንተርናሽናል ሆቴል ባለ 5 ኮከብ ደረጃን አገኘ፡፡ ሁኔታውን አስመልክቶ ሰሞኑን በሆቴሉ በተካሄደው ሥነ ስርዓት ላይ እንደተገለፀው፤ ሆቴሉ ዓለም አቀፋዊ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት ለደንበኞቹ ሲሰጥ ቆይቶ በቅርቡ በተካሄደ ፍተሻና ቁጥጥር መስፈርቱን አሟልቶ የተገኘ በመሆኑ ባለ 5 ኮከብ ደረጃ ተሰጥቶታል፡፡ የሆቴሉ ባለቤት አቶ ጌታሁን በሻህ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ሆቴሉ አሁን ላለበት ደረጃ እንዲበቃ ቤተሰቦቻቸውና መላው ሠራተኞች የከፈሉት መስዋዕትነት ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡ ሆቴሉ ባለ 5 ኮከብ ደረጃ ያለው መሆኑ ለእሳቸውም ሆነ ለሆቴሉ ሠራተኞች ከፍተኛ ደስታ እንደፈጠረላቸው ጠቅሰው፤ በቀጣይም ደንበኞቻቸውን በጥራትና በብቃት ለማስተናገድ ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል።

Read 2807 times