Sunday, 25 June 2017 00:00

“የአሸናፊነት ጉዞ ወደ ስራ ፈጠራ” የኮሌጅ ቶክ ሾው ሊጀመር ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በስራ ፈጠራ፣ አዲስ ቴክኖሎጂ በመፍጠርና በመቅዳት የተለያየ ውጤታማ ደረጃ ላይ የደረሱ ስኬታማ ሰዎች ልምዳቸውን የሚያካፍሉበት “የአሸናፊነት ጉዞ ወደ ስራ ፈጠራ፣ ቴክኖሎጂ መቅዳት፣ አዳዲስ ቴክኖሎጂ ማፍለቅና ኢንተርፕረነርሺፕ” የተሰኘ የኮሌጅ ቶክ ሾው ሊጀመር ነው፡፡ ቶክ ሾውን የሚያቀርበው ኤዲቲ የንግድ ፕሮሞሽን አገልግሎት ሲሆን ይህ ቶክ ሾው የሚካሄደው ከሰኔ 2009 እስከ ሰኔ 2010 ለአንድ ዓመት እንደሆነ አዘጋጁ ገልጻል፡፡
ኮሌጅ ቶክ ሾው ዝግጅቱ በአዲስ አበባ በሚገኙ 13 የመንግስትና የግል ቴክኒክና ሞያ ኮሌጆች እንደሚካሄድም ለማወቅ ተችሏል፡፡ ዋና አላማው በአሁኑ ወቅት በተለያዩ ኮሌጆች በተለያዩ ደረጃዎች የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ላይ የሚገኙ ተማሪዎች ተመርቀው ሲወጡ ቴክኖሎጂን በመቅዳት፣ አዲስ በመፍጠርና በመመራመር የራሳቸውን ስራ ውጤማ ሆነው እንዲሰሩ፣ የሚገጥማቸውን ችግሮች በምን መልኩ ማለፍ እንዳለባቸውና በአጠቃላይ ውጤታማነት ዙሪያ ልምድ ካላቸው ሰዎች ልምድ እንዲቀስሙ ማድረግ ነው ተብሏል፡፡

Read 3520 times