እናት የማስታወቂያ ድርጅት ከጀርመን የባህል ማዕከል (ጎተ) ጋር በመተባበር ነገ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በብሔራዊ ቤተ መፃህፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ “አለመኖር” በተሰኘው የዶ/ር ዳዊት ወንድም አገኝ መፅሐፍ ላይ ውይይት ያካሂዳል፡፡ በእለቱ ለውይይት የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት የስነ-ፅሁፍ ባለሙያው አቶ በአካል ንጉሴ እንደሆኑ የገለፀው እናት የማስታወቂያ ድርጅት ፍላጎት ያለው በውይይቱ ላይ እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርቧል፡፡