Sunday, 02 July 2017 00:00

“የተራራው ምርኮኞች” በድጋሚ ታትሞ ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(10 votes)

  እ.ኤ.አ በ1972 ጥቅምት ወር መግቢያ ላይ የኡራጓይ የአየር ሀይል የመጓጓዣ አውሮፕላን የአንድ የራግቢ ክለብ ተጫዋቾችን እና ደጋፊዎቹን አሳፍሮ ከዋናው ከተማ ከሞንቲ ቪዲዮ ወደ ቺሊ ዋና ከተማ ሳንቲያጎ በመብረር ላይ እያለ በከፍተኛነቱ ከሚታወቀው አንድስ ተራራ ላይ ወድቆ የራግቢ ተጫዋቾቹና ደጋፊዎቻቸው ለ71 ቀናት በበረዶ ላይ ያሳለፉትን ስቃይ ከስቃዩ ተረፉትንና ህይወታቸው ያለፈውን ተጓዦች ጉዳይ የሚያወሳው የተራራው ምርኮኞች መፅሐፍ በድጋሚ ታትሞ ለንባብ በቃ፡፡ በደራሲ ፒየር ፖል ሪድ የተፃፈውና በሀዲስ እንግዳ አይቼህ የተተረጎመው ይህ መፅሐፍ እውነተኛ ታሪኩ አጃኢብ ያሰኘና አ ደጋውም የ ዓለም አቀፍ የ ዜና ሽፋን ያገኘ ሲሆን ታሪኩ ወደ መፅሐፍና ወደ ፊልም ተቀይሮ ብዙ አንባቢና ተመልካች ማግኘቱ የሚታወስ ነው፡፡ መፅሐፉ በ321 ገፅ ተፅፎ በ150 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

Read 2561 times