ቻይና በትልቅነቱ በአለማችን ቀዳሚነቱን ይይዛል የተባለውና በአመት 45 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለውን አዲሱ የቤጂንግ የአውሮፕላን ማረፊያ ጣቢያ በደቡባዊ ዳዢንግ አውራጃ እየገነባች ሮይተርስ ዘግቧል፡፡በ700 ሺህ ስኩየር ሜትር ቦታ ላይ የሚያርፈው ይህ ግዙፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጣቢያ ከሁለት አመታት በኋላ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታው ተጠናቅቆ በአራት የማኮብኮቢያ መንገዶች አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር የጠቆመው ዘገባው፣ በቀጣይም ሌሎች ሁለት ማኮብኮቢያዎች እንደሚጨመሩለትና የማስተናገድ አቅሙ ወደ 100 ሚሊዮን ከፍ እንደሚል ገልጧል፡፡
በታዋቂው አርክቴክት ዛሃ ሃዲድ ዲዛይን የተደረገው አዲሱ የቤጂንግ የአውሮፕላን ማረፊያ ጣቢያ፣ የመንገደኞችን መስተንግዶ የሚያቀላጥፍና በርካታ አውሮፕላኖችን ያለ አንዳች ችግር የሚያስተናግድ እንደሆነም ተነግሯል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ