Monday, 10 July 2017 00:00

ቴስላ በዋጋ እጅግ ርካሽዋን የመጀመሪየዋ የኤሌክትሪክ መኪና አመረተ

Written by 
Rate this item
(5 votes)

    ታዋቂው የአሜሪካ ኩባንያ ቴስላ እስካሁን ከተሰሩት ሁሉ በዋጋ አነስተኛው የተባለውን የመጀመሪያውን ቴስላ ሞዴል 3 የኤሌክትሪክ መኪና በትናንትናው ዕለት አምርቶ ማውጣቱን የኩባንያው ዋና ስራ አስፈጻሚ ቢሊየነሩ ኤለን ሙስክ አስታውቀዋል፡፡ ቴስላ ሞዴል 3 ተባለቺው በኤሌክትሪክ ሃየል የምትንቀሳቀሰውና አንድ ጊዜ ቻርጅ በመደረግ እስከ 215 ማይል ርቀት መጓዝ ትችላለች የተባለቺው አምስት ተሳፋሪዎችን የመያዝ አቅም ያላት አዲሷ የኩባንያው መኪና በ35 ሺህ ዶላር ለገበያ እንደቀረበች ሚረር ድረገጽ ዘግቧል፡፡
ኩባንያው የአሌክትሪክ መኪና ለማምረት የሚያስችለውን ህጋዊ ፈቃድ ያገኛል ተብሎ ከሚጠበቅበት ጊዜ በሁለት ሳምንታት ቀደም ብሎ ማግኘቱን የዘገበው ሚረር ድረገጽ፣ እስከ ሶስት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ 32 መኪኖችን፣ እስከ መስከረም ወር ደግሞ 1ሺህ 500 መኪኖችን አምርቶ ለደንበኞቹ ለማስረከብ ስራ መጀመሩን ገልጧል፡፡
ቴስላ ኩባንያ የማምረት አቅሙን በከፍተኛ ሁኔታ በማሳደግ እስከሚቀጥለው አመት ታህሳስ ወር ድረስ በወር 20ሺህ መኪኖችን የማምረት አቅም ላይ እንደሚደርስም ተነግሯል፡፡
ኩባንያው ባለፈው የፈረንጆች አመት 2016 ብቻ ከ25 ሺህ በላይ ሞዴል ኤክስ እና 51 ሺህ ያህል ሞዴል ኤስ የተባሉ መኪኖቹን ለደምበኞቹ በመሸጥ 7 ቢሊዮን ዶላር ያህል ገቢ ማግኘቱንም ዘገባው አስታውሷል፡፡

Read 3890 times