በደራሲ አሰግድ መኮንን የተፃፈውና እውነተኛ ታሪክ የሆነው ‹‹የቃል ፅናት›› መፅሐፍ ዛሬ ከቀኑ 9፡00 ጀምሮ በአፋረንሲስ ኢንተርናሽናል ሆቴል ይመረቃል።መፅሀፉ ብሩክ ከበደ ስለተባሉ የጦር አርበኛ ታሪክና አሟሟት፣ ከመንዝና ግሼ ስንሰለታማ ተራሮች ጀምረው የተዋጉባቸውን ቦታዎች የጦርነቱን ሁኔና ይተርካል ተብሏል፡፡ በ230 ገፆች የተቀነበበው መፅሀፉ፤ በ81 ብር ከ60 ሳንቲም ለገበያ ቀርቧል፡፡
ፀሀፊው ከዚህ ቀደም ‹‹ኮብላይ››፣ ‹‹ጥብቅ ምስጢር››፣ ‹‹ነፀብራቅ››፣ ‹‹ማጎርሚ ሳቢብ››፣ ‹‹እኔና ህይወቴ›› ፣‹‹ከኢትዮጵያ ወንዞች ማዶ›› እና ‹‹ሞትን
ቀደምኩት›› የተሰኙ መፅሀፍትን ለንባብ ማብቃታቸው የሚታወስ ሲሆን ‹‹የቃል ፅናት›› 8ኛ መፅሀፉ እንደሆነ ታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና